Get Mystery Box with random crypto!

የአንተን በኑሮ ውድነት መጠበስና ብስቁልና ካልደረሰባቸው እንዴት ሊረዱልህ ይችላሉ? እንዳይደርስ | ዘሪሁን ገሠሠ

የአንተን በኑሮ ውድነት መጠበስና ብስቁልና ካልደረሰባቸው እንዴት ሊረዱልህ ይችላሉ?

እንዳይደርስባቸው ደግሞ ከዘረፋና ምዝበራው ባሻገር በዚህ መልኩ ህግ አውጥተው ራሳቸውን ይታደጋሉ፡፡

☞ በአዲስአበባ ለተሾሙ በየደረጃው ያሉ አመራሮች ከተማ አስተዳደሩ ቤት ያመቻቻል!

ከመደበኛ ደመወዛቸው ውጪ የሚከፈል የኃላፊነት አበልን በተመለከተ ፦

☞ ለከንቲባውና ለምክር ቤት አፈ-ጉባኤ - 18 ሺህ ብር

☞ ለም/ከንቲባውና በምክትል ማዕረግ ለተሾሙ አመራሮች - 17 ሺህ ብር

☞ ለከተማ አስተዳደሩ ካቢኔዎችና በቢሮ ሀላፊነት ደረጃ ለተሾሙ - 16 ሺህ ብር

☞ በም/ኃላፊዎች ፥ ኮሚሽነሮች ወዘተርፈ - 15ሺህ ብር

☞ ፅ/ቤት ኃላፊዎች ፥ የወረዳ ስራ አስፈፃሚዎች ፣ የኮሌጅ ዲኖች ፥ ወዘተርፈ - 14 ሺህ ብር

☞ የወረዳ ም/ኃላፊዎችና መሠሎች - 13ሺህ ብር

☞ የወረዳ ካቢኔ አባላትና በዚያ ደረጃ ለተሾሙ - 12ሺህ ብር ይከፈላቸዋል፡፡

ይቺን አሰራር ክልሎችና በተዋረድ ያሉት መንግስታዊ መዋቅሮችም እንደአዲስአበባ ራሳቸው ህግ አውጥተው በማፅደቅ ሲገለገሉ የሚያሳይ መረጃ ባላገኝም ፥ በግልፅም በውስጥም እንደሚሰሩባት የሚታመን ነው፡፡

ኢትዮጵያ መሪዎቿና ሰፊው ህዝቧ የተራራቁት በዚህ መልኩ ነው! ሠፊው ህዝብ አክርማና ስንደዶ አዋጥቶ የሰፋትን ኢትዮጵያ የተባለች ሞሰብ ፥ የሚመገቡባት ፖለቲከኞች ሲሆኑ የበይ ተመልካች የሆነውና የሚደክምላት ደግሞ ሰፊው ህዝብ ብቻ ነው!