Get Mystery Box with random crypto!

YeneTube

የሰርጥ አድራሻ: @yenetube
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 130.41K
የሰርጥ መግለጫ

መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2024-04-16 20:55:37
ማስጠንቀቂያ! ቪዲዮውን ከ 18 ዓመት በታች የሆኑ ሰዎች እንዲያዩት አንመክርም።

በሲድኒ፣ አውስትራሊያ የሚገኝ አንድ ቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ላይ እያለ አንድ ቢላዋ የያዘ ሰው በአንድ ቄስ ላይ በትናንትናው ዕለት ጥቃት ሰነዘረ።

ይሄ ሰው በዋኪሊ በሚገኘው የደጉ እረኛ ቤተክርስቲያን ቀርቦ ጳጳስ ማሪ ኢማኑኤልን ደጋግሞ በስለት ወግቷቸዋል።

ጥቃት አድራሹ ቄሱን ለመዳን የሞከሩ አራት ምእመናን ላይም ጥቃት ፈፅሟል። ቄስ ማሪ ኢማኑኤል ጉዳት ቢያጋጥማቸውም ከመሞት ተርፈዋል ሲሉ የሀገሪቱ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።

ይሄ ሰው ከአንድ ቀን አስቀድሞ አንድ ሰው በሲድኒ የገበያ ማእከል ውስጥ ገሎ መሰወሩም ተነግሯል።
12.9K views17:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-16 19:16:43
ጥገኝነት ጠያቂዎችን ወደ ሩዋንዳ ለማዛወር እንግሊዝ የነደፈችው ረቂቅ ሕግ ሊጸድቅ ነው!

ብሪታንያ ጥገኝነት ጠያቂዎችን ወደ ሩዋንዳ ለማዛወር የያዘችው እና ከፍ ያለ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር የታመነው ዕቅድ የሃገሪቱ ሕግ ሊሆን ተቃርቧል። የዕቅዱ ተቃዋሚዎች በአንጻሩ ስደተኞቹን በኃይል ከአገር የማስወጣቱን ውጥን ማገድ የሚችል አዲስ የሕግ መቋቋሚያ ለማበጀት ጥረት ይዘዋል።

የጠቅላይ ፍርድ ቤቱን እገዳ ተጽዕኖ ለማስቀረት እና በላይኛው ምክር የቀረበውን ተቃውሞ ለመቋቋም የታለመው ይህ ሕግ በያዝነው ሳምንት በሃገሪቱ ፓርላማ ይድቃል ተብሎ ተጠብቋል።

‘የሩዋንዳ ዕቅድ’ የሚል ቅጽል የተሰጠው ይህ ውጥን ጠቅላይ ሚንስትር ሪሺ ሱናክ ‘ሕገ ወጥ ስደተኞችን ወደዚያች አገር የሚያጓጉዙ ጀልባዎች እንቅስቃሴ’ ለማስቆም ለገቡት ቃል ‘ወሳኝ እርምጃ ነው’ ተብሏል።

ጉዳዩን አመልክቶ አስተያየት የሰጡት የሱናክ ቃል አቀባይ ዴቭ ፓሬስ ትናንት ሲናገሩ "የእንግሊዝ ፓርላማ በያዝነው ሳምንት በሕገ ወጥ አስተላላፊዎች ከፍተኛ እንግልት እና ብዝበዛ የሚፈጽምባቸውን ሰዎች ህይወት የሚታደግ ህግ የማጽደቅ እድል ያገኛል" ብለዋል ። “አሁን ባለው አካሄድ መቀጠል እንደማንችል ግልፅ ነው። በመሆኑም ይህ ሁኔታ የሚለወጥበት ጊዜው አሁን ነው” ሲሉም አክለዋል።

በአነስተኛ ጀልባዎች ተጓጉዘው የእንግሊዝ ቻናልን በማቋረጥ ከዚያ የሚደርሱትን ጥገኝ ነት ጠያቂዎች ወደ ምሥራቅ አፍሪካዊቱ አገር ለማዛወር እና በቋሚነትም ኑሯቸውን ከዚያ እንዲያደርጉ በማቀድ ሁለቱ አገሮች የተፈራረሙት ስምምነት ሁለት ዓመታት አስቆጥሯል። በፍርድ ቤት የታገደው ዕቅድ እንግሊዝን በትንሹ 470 ሚሊዮን ዶላር ሊያስወጣት እንደሚችልም ተገምቷል።

Via VoA
@YeneTube @FikerAssefa
13.6K views16:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-16 17:07:26
በቀጣዩ የፈረንጆቹ 2025 ዓመት፤ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ 6.5 በመቶ ያድጋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ይፋ አደረገ።

IMF ዛሬ ማክሰኞ ሚያዝያ 8፤ 2016 ይፋ ያደረገው ትንበያ፤ ከዘንድሮው አኳያ ሲነጻጸር የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በሚቀጥለው ዓመት አነስተኛ መነቃቃት እንደሚታይበት የሚጠቁም ነው።

በተያዘው የፈረንጆቹ ዓመት፤ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በ6.2 በመቶ ያድጋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ድርጅቱ ባለፈው ዓመት ባወጣው ተመሳሳይ ትንበያ ይፋ አድርጎ ነበር። የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት ትንበያ የኢትዮጵያ መንግስት ከሚጠብቀው ዝቅ ያለ ነው። በኢትዮጵያ መንግስት ትንበያ መሰረት፤ በ2016 ዓ.ም. የሀገሪቱ ኢኮኖሚ በ7.9 በመቶ ያድጋል ተብሎ ይጠበቃል። 

(ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
@YeneTube @FikerAssefa
13.5K views14:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-16 15:11:46 በአዲስ አበባ ከተማ በተወሰኑ አካባቢዎች እየተከናወኑ በሚገኙ የኮሪደር ልማት ሥራዎች ምክንያት ዝግ ሆነው የቆዩ መንገዶች ለተሽከርካሪ ክፍት መደረጋቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ።

በዚህም መሰረት፡-

•  ከደጃች ውቤ በአፍንጮ በር ወደ ራስ መኮንን ድልድይ

•  ከባሻወልዴ ችሎት በቱሪስት ሆቴል ራስ መኮንን ድልድይ አፍንጮ በር

•  ከዳኑ ሆስፒታል እስከ ቱሪስት ሆቴል በመውጣት ወደ ራስ መኮንን ድልድይ አፍንጮ በር

•  ከአራዳ መስተዳደር ወደ ዳኑ ሆስፒታል መውረጃ በአንድ አቅጣጫ ብቻ አሽከርካሪዎች መጠቀም እንደሚችሉ ከአዲስ አበባ ፖሊስ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ እየተከናወኑ ባሉ የልማት ሥራዎች ምክንያት ለአጭር ሆነ ለረጅም ጊዜ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ በጥብቅ መከልከሉን ፖሊስ አስታውቋል፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
13.7K views12:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-16 12:34:10
ኢትዮጵያ አሁን ላይ ያሏት የሚሊየነሮች ቁጥር በአጠቃላይ 2,700 መድረሱን በዘርፉ ላይ የተደረገ አንድ ሪፖርት አመላከተ

ኢትዮጵያ በአሁን ጊዜ ወደ 2,700 የሚጠጉ ሚሊየነሮች እንዳሏት የገለፀዉ ይህ የአፍሪካ ሀብት ሪፖርት ሀገሪቷ በዚህ የስነ ህዝብ እድገት ዉስጥ ጠንካራ እንድገት እንደሚኖረዉ ትንበያውን አስቀምጧል።

በ 2024 የወጣዉ የአፍሪካ ሀብት ሪፖርት ዘጠኛ እትሙ ላይ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አዳዲስ ገበያዎችን የሚይዘው የአህጉሪቱ ሚሊየነር ህዝቧ በሚቀጥሉት አስርት አመታት ዉስጥ በ 65% ከፍ ሊል እንደሚችል ግምቱን አስቀምጧል ።

አሁን ላይ በአፍሪካ ያለዉ አጠቃላይ የኢንቨስትመንት ሀብት 2.5 ትሪሊዮን ዶላር መድረሱ የተነገረ ሲሆን ኢትዮጵያ በዚህ ኢኮኖሚ እድገት ዉስጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማድረጓ ነዉ ይህ ሀተታ የሚያመላክተዉ።

Via:- Capital
@Yenetube @Fikerassefa
13.5K views09:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-16 11:30:12
በኢትዮጵያ 56 በመቶ የሚሆኑት ተማሪዎች ምንም አይነት ቃላት ማንበብ እንደማይችሉ አንድ ጥናት አመላከተ፡፡

የሀገር አቀፍ ፈተናዎች ኤጀንሲ አደረጉት ባለዉ ዓመታዊ ጥናቱ ላይ እንደገለፀው በኢትዮጵያ 56 በመቶ የሚሆኑ የ 2ኛ እና የ 3ኛ ክፍል ተማሪዎች ምንም አይነት ቃላት ማንበብ እንደማይችሉ አረጋግጫለሁ ብሏል።

የሀገር አቀፍ ፈተናዎች ኤጀንሲ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ሲያከናዉን የቆየዉን ጥናት ይፋ አድርጓል ። በዚህም ከትግራይ ክልል በስተቀር በተለያዩ የሀገሪቱ ክልሎች የሚገኙ 401 ትምህርት ቤቶች እና በ 16 ሺህ ተማሪዎች ላይ በተደረገ ጥናት ዉጤቱ መገኘቱን አስታዉቀዋል።

ይህ ቁጥር ከባለፉት አመታት ጋር ሲነፃፀር በመጠኑ መሻሻል አሳይታል የተባለ ሲሆን ከሁለት አመት በፊት የተደረገው ጥናት ምንም ማንበብ የማይችሉት 63 በመቶዎች እንደነበሩ ጥናቱ አመላክቷል።
@Yenetube @Fikerassefa
12.7K viewsedited  08:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-16 11:25:18
አስደሳች ዜና ለወላጆች

         Ace Tutors
 
  በማንኛውም የት/ት ደረጃ ለሚገኙ ልጆችዎ ብቁ የሆኑ አስጠኚዎች አዘጋጅተናል


- ለብሄራዊ እና ለት/ቤት ፈተና እናዘጋጃለን
- ብቁ በሆኑ ወንድ እና ሴት አስጠኚዎች
- ለሁሉም የት/ት ደረጃ ከ Kg - 12ተኛ ክፍል


ለበለጠ መረጃ
በ0943909174 ይደውሉ

@acetutorshr
@acetutorshr
12.7K views08:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-15 19:22:46
የኢትዮጵያ እና ኬንያ አትሌቶች ሆን ብለው ቻይናዊ ሯጭ እንዲያሸንፍ በማድረግ ተከሰሱ!

አንድ የኢትዮጵያ እና ሁለት ኬንያውያን አትሌቶች ቻይናዊ ሯጭ የቤይጂንግ ግማሽ ማራቶንን እንዲያሸንፍ አድርገዋል ተብለው ምርመራ ተጀመረባቸው።

የውድድሩ አዘጋጅ ቤይጂንግ ስፖርትስ ቢሮ ክስተቱን እየመረመርኩ ነው ሲል ለፈረንሳይ የዜና ወኪል - ኤኤፍፒ ተናግሯል። ኢትዮጵያዊው አትሌት ደጀኔ ኃይሉ ቢቂላ እንዲሁም ኬንያውያኑ ሮበርት ኬተር እና ዊሊ ማናንጋት ቻይናዊው አትሌት ሂ ጂ እንዲያሸንፍ ያደረጉበት ሁኔታን የተመለከቱ ቻይናውያን “ስፖርታዊ ሥነ ምግባር የሌለበት አሳፋሪ ተግባር” ሲሉ ገልጸውታል።

ሦስቱ አትሌቶች ከውድድሩ መጀመሪያ አንስቶ እስከ ማጠናቀቂያው ድረስ ቻይናዊውያን አትሌት አጅበው ሲሮጡ ነበር።በማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ በስፋት በተጋራው ቪዲዮ ላይ የውድድሩ መጨረሻ አካባቢ ሦስቱ የምሥራቅ አፍሪካ አትሌቶች ፍጥነታቸውን በመቀነስ ቻይናዊው አትሌት እንዲያልፋቸው በእጃቸው ሲጠቁሙት ይታያሉ።

በመጨረሻም የመላው እስያ ጨዋታዎች የማራቶን የወርቅ ሜዳሊያ አሸናፊው ቻይናዊ አትሌት ሦስቱን የምሥራቅ አፍሪካ አትሌቶች አስከትሎ በአንድ ሰከንድ ልዩነት ብቻ ውድድሩን አሸንፏል። የውድድሩ አዘጋጆች ለኤኤፍፒ “ምርመራ እያደረግን ነው። ምርመራችን ሲጠናቀቅ ውጤቱን ይፋ እናደርጋለን” ብሏል።

@YeneTube @FikerAssefa
14.5K views16:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-15 18:46:32
ታዋቂው አቡነ ማር ማሪ ኢማኑዔል በቀጥታ የሚተላለፍ ትምህርት እየሰጡ ሳሉ በስለት ተወጉ!

በአውስትራሊያ ሲድኒ በቀጥታ በኢንተርኔት እየተላለፈ የነበረ መንፈሳዊ ትምህርት እየሰጡ የነበሩት አቡን እና ሌሎች ምዕመናን በስለት ተወጉ።ይህ የሆነው ዋኬሌ በሚገኘው ክራይስት ዘ ጉድ ሼፐርድ በተሰኘው ቤተ-ክርስቲያን በአውስትራሊያ ሰዓት በቆጣጠር ዛሬ ሰኞ አመሻሽ ላይ በነበረ ሥነ-ሥርዓት ነው።

በስለት ጥቃት ከተፈጸመባቸው መካከል የሆኑት አቡነ ማር ማሪ በተለያዩ የማኅበራዊ ሚዲያ መድረኮች ላይ በእንግሊዝኛ በሚያርቧቸው መንፈሳዊት ትምህርቶቻቸው ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ በብዙዎች ዘንድ ተደማጭ ናቸው።ጥቃቱን ተከትሎ በርካታ ሰዎች በስለት ተወግተዋል የሚል ሪፖርት የደረሰው ፖሊስ ወደ ሥፍራው ተሰማርቶ ሁኔታውን ያጣራ ሲሆን፣ የሰዎች ሕይወትን ለአደጋ የሚዳርግ ጉዳት አልደረሰም ብሏል።

ፖሊስ አክሎ እንደገለጠው አንድ ግለሰብ በቁጥጥር ሥር ውሎ አድራሻው ወዳልተገለጠ ሥፍራ ተወስዷል።ከጥቃቱ በኋላ በርካታ ሰዎች የተሰባሰቡ ሲሆን ቢቢሲ ያላጣራቸው የማኅበራዊ ሚድያ ቪድዮዎች እንደሚያሳዩት አንዳንድ ሰዎች በሕንፃው እና በአደጋ ጊዜ ሠራተኞች መኪናዎችን ላይ ጥቃት አድርሰዋል።ሥፍራው በከፍተኛ ሁኔታ እየተጠበቀ እንደሆነ የገለጠው ፖሊስ ሰዎች ወደዚያ አካባቢ እንዳይሄዱ አሳስቧል።

የአካባቢው ፖሊስ ጥቃት የደረሰባቸው አቡን ስማቸው ማር ማሪ ኢማኑዔል እንደሆነ አሳውቋል። የኢስተርን ኦርቶዶክስ ቤተ-ክርስቲያንም ከፖሊስ ዘገባ በኋላ የሃይማኖት አባቱን ማንነት ይፋ አድርጓል።ቤተ-ክርስቲያኗ በሰጠችው መግለጫ አባ ኢሳክ የተባሉ ቄስም ጉዳት እንደደረሰባቸው አሳውቋል። ሁለቱም የሃይማኖት አባቶች ለሕክምና ወደ ሆስፒታል ተልከዋል።

[BBC]
@YeneTube @FikerAssefa
14.4K views15:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-15 16:11:42
ኤክሳይዝ ታክስ በሚከፈልባቸዉ እንደ አልኮል መጠጦች ፣ ሲጋራ እና የታሸገ ዉሃ ላይ ላይ ቴምብር እንዲለጠፍ የሚያስገድደዉ መመሪያ ወጣ!

የገንዘብ ሚኒስትር የኤክሳይዝ ቴምብር አስተዳዳር ስርዓትን ለመወሰን የሚያስችለውን መመሪያ ከሰሞኑ አዉጥቷል።በዚህ መመሪያዉ የኤክሳይዝ ታክስ በሚከፈልባቸዉ እቃዎች ማለትም የአልኮል መጠጦች፤ አልኮልና እና አልኮል አልባ ቢራ፤  ሲጋራ፤ ሲጋሪልስ፤ ትምባሆ ፣ የታሸገ ውሃና ሌሎች ኤክሳይዝ ታክስ በሚከፈልባቸዉ ዕቃዎች ላይ ተግበራዊ ይደርጋል።

የኤክሳይዝ ቴምብር  በወረቀት፤ በዲጂታል ወይም ሚኒስቴሩ በሚወስነው መልክ የተዘጋጀና የኤክሳይዝ ታክስ በሚከፈልባቸው እቃዎች ላይ የሚታተም ወይም የሚለጠፍ ቴምብር ማለት እንደሆነ በዝርዝር ያስቀምጣል።

የገንዘብ ሚኒስቴር ባወጣዉ በዚህ መመሪያ የኤክሳይዝ ታክስ በሚከፈልባቸው እቃዎች አቅርቦት ሰንሰለት ውስጥ ተሳታፊ የሆነ ማናቸውም ላኪ በእጁ የሚገኙትን የኤክሳይዝ ታክስ የሚከፈልባቸው እና የኤክሳይዝ ቴምብር ያልተለጠፈባቸው ወይም ምልክት ያልተደረገባቸዉን ዕቃዎችን
ለገበያ ማዋል አይችልም።

[Capital]
@YeneTube @FikerAssefa
14.7K views13:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ