Get Mystery Box with random crypto!

Tikvah-University

የሰርጥ አድራሻ: @tikvahuniversity
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 212.34K

Ratings & Reviews

5.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2024-04-22 18:38:01
የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ሴኔት የተቋሙ የዘንድሮ ተመራቂ ተማሪዎች በሰኔ 2016 ዓ.ም ወይም በጥር 2017 ዓ.ም የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና ለመውሰድ በግለሰብ ደረጃ እንዲወስኑና በውሳኔያቸው መሰረት ለፈተው እንዲቀመጡ ዩኒቨርሲቲው ዕድል እንዲፈጥር
ወስኗል፡፡

በዚህም በሰኔ ወር የመውጫ ፈተና ለመውሰድ ፍላጎቱ ያላቸው ተመራቂ ተማሪዎች ስም ዝርዝር በአስቸኳይ ወደ ትምህርት ሚኒስቴር መላክ ሰላለበት ተፈታኞች እስከ ሚያዝያ 17/2016 ዓ.ም መመዝገብ ይጠበቅባቸዋል ተብሏል፡፡

በተጠቀሰው ግዜ ውስጥ ስማቸውን ያላስመዘገቡ ተመራቂ ተማሪዎች በጥር 2017 ዓ.ም ፈተናውን ለመውሰድ እንዳቀዱ ተደርጎ እንደሚወሰድ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

@tikvahuniversity
18.6K views15:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-22 18:37:47
የራያ ዩኒቨርሲቲ አሰራርን የሚያዘምኑ ሦስት መተግበሪያዎችን የተቋሙ መምህራን እና ባለሙያዎች አበልፅገው ሥራ አስጀመሩ፡፡

የበለፀጉት መተግበሪያዎች የንብረት አስተዳደር መረጃ ስርዓት፣ የፈተና አስተዳደር ስርዓት ፖርታል እና የራያ ዩኒቨርሲቲ ድረ-ገፅ መሆናቸው ተገልጿል፡፡

መተግበሪያዎቹ ብክነት ለመቀነስ፣ ደህንነት ለማስጠበቅ፣ እንዲሁም ቀልጣፋ እና ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት ያግዛሉ ተብሏል፡፡

የፈተና አስተዳደር ስርዓት ፖርታሉን በመጠቀም ባሳለፍነው ጥር ለዩኒቨርሲቲው የ2016 ዓ.ም ዕጩ ተመራቂዎች ውጤታማ የሞዴል ፈተና ተሰጥቶ እንደነበር ተነስቷል።

@tikvahuniversity
17.3K views15:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-22 18:20:35
#የቻናል_ጥቆማ

ለኢንጂነሪንግ ተማሪዎች እና Construction ዘርፍ ላይ ለተሰማራችሁ በሙሉ

የኮንስትራክሽን፣ ሲቪል ኢንጂነሪንግ፣ የአርክቴክቸር ተማሪ ነዎት? በጠቅላላ ኮንስትራክሽን የተሰማሩ ባለሙያ ነዎት?

በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ የሌክቸር ትምህርቶች፣ መፃሕፍቶች፣ ቪዲዮዎች እና ጠቃሚ የኮንስትራክሽን ዕውቀቶች ለማግኘት ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን ይቀላቀሉን!

ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያዎች፣
አዲስ የሚወጡ የግንባታ ጨረታዎች፣
እጅግ ጠቃሚ የኮንስትራክሽን መረጃዎች፣
በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ሌክቸር የምታገኙበት፡፡

Join Us :-

on Telegram

https://t.me/ethioengineers1
https://t.me/ethioengineers1

on TikTok

tiktok.com/@ethiocons
tiktok.com/@ethiocons
16.9K views15:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-22 12:29:13
ትምህርት ሚኒስቴር ለ 50,000 መምህራን እና የትምህርት አመራሮች የብቃት ስልጠና ሊሰጥ ነው፡፡

በመጪዎቹ ሐምሌ እና ነሐሴ ወራት የሚሰጠው ስልጠናው፤ የቅድመ አንደኛ ደረጃ፣ የአንደኛ ደረጃ እና የሁለተኛ ደረጃ መምህራንን አቅም ለማሳደግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

42,000 መምህራን ለ120 ሰዓት እንዲሁም 8,000 የትምህርት አመራሮች ለ60 ሰዓት ስልጠና እንደሚሰጣቸው በሚኒስቴሩ የመምህራንና የትምህርት አመራር መሪ ሥራ አስፈጻሚ ሙሉቀን ንጋቱ (ዶ/ር) ለኤፍቢሲ ተናግረዋል።

መምህራኑ በሚያስተምሩበት ትምህርት ውጤታማነታቸውን የሚጨምር የማስተማር ስነ-ዘዴ (ፔዳጎጂ) ስልጠና የሚሰጣቸው ሲሆን፤ ስልጠናቸውን ሲያጠናቅቁ ፈተና እንደሚወስዱ መሪ ሥራ አስፈጻሚው ገልፀዋል፡፡

ስልጠናው በተመረጡ ዩኒቨርሲቲዎች እና ኮሌጆች እንደሚሰጥ ተጠቁሟል፡፡

@tikvahuniversity
27.3K views09:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-22 12:12:29
#SamiTech

አዳዲስ ላፕቶፕች ከአንድ ዓመት ዋስትና ጋር!!
@samcomptech

በአገልግሎት አሰጣጣችንና በዕቃዎቻችን ጥራት ላይ ደንበኞቻችን ምስክሮች ናቸው።
ዛሬም ብዛት እንዲሁም ጥራት ሳንቀንስ እያስተናገድን እንገኛለ!

ለቢሮዎች፣ ለተማሪዎች፣ ለዲዛይን ባለሙያዎች፣ ለጌመሮች፣ ወ.ዘ.ተ.

አቅምን ካገናዘቡ እስከ ቅንጡ ላፕቶፖች ይህ ቀረ ሳይሉ የሚያገኙበትን ሱቃችንን ይጎብኙ! የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ ባሉበት ሆነው ይዘዙን እናደርሳለን።

የዕቃዎች ዋጋ፣ ዓይነት እና አድራሻ ለማግኘት @samcomptech ተጭነው በቴሌግራምዎ ማየት ይችላሉ።

@sww2844
0928442662
0940141114

https://t.me/samcomptech
26.1K views09:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-22 08:28:11
#MoE

በሰኔ ወር 2016 ዓ.ም የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና ለመጀመሪያ ጊዜ የሚፈተኑ ተፈታኝ ተማሪዎች እያንዳንዳቸው የአገልግሎት ክፍያ 500.00 (አምስት መቶ) ብር ብቻ የሚከፍሉ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር ለሁሉም የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በፃፈው ደብዳቤ አሳውቋል።

በዚህም ተፈታኞች የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሒሳብ ቁጥር 1000553176097 በመጠቀም እስከ ማክሰኞ ሚያዚያ 15/2016 ዓ.ም ድረስ ለትምህርት ሚኒስቴር ገቢ እንዲያደርጉ አሳስቧል።

ተፈታኞች የከፈሉበትን ደረሰኝ ኮፒ በኢሜይል አድራሻ antedefar@gmail.com እና lakbt2013@gmail.com መላክ ይኖርባቸዋል።

(ተጨማሪ መረጃ ከተያያዘው ደብዳቤ ይመልከቱ።)

@tikvahuniversity
37.0K views05:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-20 19:31:53
ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሶሻል ወርክ ትምህርትን በሦስተኛ ዲግሪ ፕሮግራም መስጠት ሊጀምር ነው።

የዩኒቨርሲቲው ሶሻል ወርክ ትምህርት ክፍል ፕሮግራሙን ለመክፈት በሀገር አቀፍ ደረጃ የፍላጎት የዳሰሳ ጥናት ማካሔዱ ተገልጿል።

ፕሮግራሙን ለማስጀመር አዲስ ስርዓተ ትምህርት በማዘጋጀት በባለሙያዎች ሲያስገምግም ቆይቷል።

በዚህም የተሰጡትን ማስተካከያዎች በማካተት የማረጋገጫ አውደ ጥናት አካሒዷል፡፡

@tilvahuniversity
16.4K views16:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-20 14:19:19
ታዳጊዎቹ የድረ-ገፅ አበልፃጊዎች

ጎዶሊያስ ሙሉጌታ እና ሰላዲን መራዊ በአቤም ዩዝ አካዳሚ የሰባተኛ ክፍል ተማሪ ናቸው።

ታዳጊዎቹ የግለሰብ መረጃን ወይም 'CV' የሚያደራጅ ድረ-ገፅ አበልፅገዋል።

ድረ-ገፁ፤ ሰዎች ሥራን ለመቀጠር የሚያስገቡት የራስ መግለጫ 'CV'' በእጅ ስልካቸው ላይ እንዲያገኙና በማንኛውም ሰዓት ለሚፈልጉት ቀጣሪ ማስገባት የሚያስችል ነው።

ድረ-ገፁ የግለሰቡን የትምህርት ደረጃ፣ አድራሻ፣ ክህሎቶች እና የሰዎችን ምስክርነትን ማካተት የሚያስችል መሆኑን ታዳጊዎቹ ተናግረዋል።

ድረ-ገፁ የሰዎችን ብቻ ሳይሆን የድርጅቶችን መረጃ እንዲያስቀምጥ ተደርጎ የተዘጋጀ መሆኑንም ታዳጊዎቹ አስረድተዋል።

ታዳጊዎቹ በአዲስ አበባ ሳይንስ ሙዚየም በተከፈተው የ'ስታርት አፕ' አውደ-ርዕይ ላይ ፈጠራቸውን አቅርበዋል። #ENA

@tikvahuniversity
25.3K views11:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-20 12:37:08
#Update

የመውጫ ፈተና መቼ ይሰጣል?

ትምህርት ሚኒስቴር ሚያዝያ 9/2016 ዓ.ም ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በፃፈው ደብዳቤ፤ የመውጫ ፈተና ከሰኔ 14 እስከ 21/2016 ዓ.ም ድረስ እንደሚሰጥ ለማወቅ ተችሏል፡፡

የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመውጫ ፈተና ለመጀመሪያ ጊዜ የሚወስዱ የቅድመ ምረቃ ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎችን መረጃ በማሰባሰብ በትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በኩል አረጋግጠው ባሳለፍነው ሳምንት ለትምህርት ሚኒስቴር መላካቸውን ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

@tikvahuniversity
28.2K views09:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-20 12:34:10
10ኛ ዙር ሙሉ የሒሳብ መዝገብ አያያዝ (Modern Accountancy and Auditing) ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን!

100% በተግባር የተደገፈ ስልጠና
የሥራ ላይ ስልጠና (Internship) የተመቻቸለት
መሠረታዊ አካውንቲንግ እና ኦዲት አሰራር፣ ሙሉ የአካውንቲንግ ሒሳብ አሰራር በፒስቺሪ ተደግፎ እና የግብር አያያዝ ትምህርቶችን አካቶ የሚሰጥ

ለበለጠ መረጃ፦  0906777799 / 0906777755

አድራሻ፦ ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ

የበለጠ ይጠብቁ ...
        ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት


Facebook | Telegram | Instagram | LinkedIn
21.6K views09:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ