የሕንድ ማላንካራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕገ ወጡን ሹመት በመቃወም መግለጫ አወጣች። ከአምስቱ ኦሪየንታል አብያተ ክርስቲያናት መካከል አንዷ የሆነችው የሕንድ ማላንካራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕገ ወጡን ሹመት በመቃወም መግለጫ አውጥታለች። ቤተ ክርስቲያኗ በመግለጫዋ በአቶ አካለ ወልድ /በቀድሞው አባ ሳዊሮስ/ ጥንታዊ የቤተ ክርስቲያንን ቀኖና በመጣስ የተፈጸመውን ሹመት በማውገዝ እንደማትቀበል አሳውቃለች። ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ያላትን ድጋፍም ገልጻለች። 19.1K viewsTadele Tibebu, 11:16