Get Mystery Box with random crypto!

Tadele Tibebu - ታደለ ጥበቡ

የቴሌግራም ቻናል አርማ tadeletibebu — Tadele Tibebu - ታደለ ጥበቡ
ርዕሶች ከሰርጥ:
Amharagenocide
Stopamharagenocide
Amharaunderattack
Statesponsoredamharagenocide
Westend
All tags
የቴሌግራም ቻናል አርማ tadeletibebu — Tadele Tibebu - ታደለ ጥበቡ
ርዕሶች ከሰርጥ:
Amharagenocide
Stopamharagenocide
Amharaunderattack
Statesponsoredamharagenocide
Westend
All tags
የሰርጥ አድራሻ: @tadeletibebu
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 71.80K
የሰርጥ መግለጫ

ማንኛውንም ሀሳብና አስተያየት በዚህ ሊንክ መላክ ይችላሉ @Tadeletibebut

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-05-10 20:23:46
15.9K viewsTadele Tibebu, 17:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-10 20:23:19 #ሼር_ፖስት! አማርኛ ቋንቋ እንደሆነ የራሡ የሆነ ሥርዓተ ድህፈት (Orthography) ያለው፣ ከፍተኛ የሆነ የሰዋሠው (Grammar) እና የሥነ-ልሣን (Linguistics) ጥናትና ምርምር የተደረገበት፣ በአፍሪካ ምድር በስነ ጽሁፍ ሀብት የበለጸገ ብቸኛውና ነባር ዓለምአቀፍ ቋንቋ ነው።

ከትግራይ ሥርዓተ ትምህርት ብታስወግደው በ2007 ዓ.ም.የአፕል የቴክኖሎጂ ማዕከል አማርኛን ከዓለም ግዙፍ ቋንቋዎች ተርታ መድቦ የቴክኖሎጂ ቋንቋ አድርጎታል።

አማርኛን ከትግራይ ብትፍቀው በ2008 ዓ.ም. የጎግል የቴክኖሎጂ ማዕከል የመተርጎሚያ ቋንቋ አድርጎታል።

እንዲያው አዲስ የጫጉላ ሽርሽር ሆናባችሁ እንጂ አማርኛ በUS አሜሪካ የመንግስት ቋንቋም ነው። በአሜሪካዋ ቨርጂኒያ ግዛት አሌክሳንድሪያ ዳሽ የሚባለው የከተማ አውቶቢስ ላይ "እንኳን ወደ #WESTEND በደህና መጣችሁ!" የሚል ጽሁፍ ማየትም የተለመደ ነው።

Dstv'ም የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና፣ የኦሊምፒክ ውድድሮችን ጨምሮ የእንግሊዝ ኘሪሚየር ሊግ ፣ የስፔን ላሊጋ ፣ የጣሊያን ሴ ሪ ኤ እንዲሁም ቻምፒየንስ ሊግ ጨዋታዎችን በአማርኛ ቋንቋ እንዲተላለፉ ከወሰነ አመት አስቆጥሯል።

ከጀርመን ታዋቂ ከሆኑት ዩኒቨርስቲዎች አንዱ የሆነው ሀምቡርግ ዩንበርሲቲ የአማርኛ ት/ ት ማስተማር ከጀመረ መቶ ዓመት አልፎታል።

ቻይና አማርኛ ቋንቋን በመጀመሪያ ዲግሪ እያስተማረች ነው። ትምህርቱ እየተሰጠ ያለው በቤጂንግ የውጭ ጥናት ዩኒቨርስቲ (BFSU) ነው።

በቅርቡ ደግሞ የፑቲን ሀገር ሩሲያ የአማርኛን ቋንቋ በሩሲያ ትምህርት ቤቶች ማስተማር ልትጀምር መሆኗን ይፋ እንዳደረገች የምናስታውሰው ነው።

እነዚህ የግንጠላ አራማጅ ዘውጌዎች ተፈራረሙ አልተፈራረሙ የሚመጣ ለውጥ የለም። ከትግራይ ሥርዓተ ትምህርት ተወገደ አልተወገደ የሚጎዳቸው እራሳቸውን እንጂ ማንንም አይጎዱም። አማርኛ እንደሆነ እንደ ሰሜን አሜሪካ የመሣሠሉ ታላላቅ ሀገሮች ውስጥ በኦፊሻል ቋንቋነት መንግሥታት እየተቀበሉት የመጣ ቋንቋ ነው።አሜሪካ ከ500 ሺህ በላይ ተናጋሪ ላለው ለተጨማሪ የሥራ ቋንቋነት በማጨት ከ10 ዓመት በፊት ነበር አማርኛ በተለያዩ የአሜሪካ ግዛቶች የሥራ ቋንቋ እንዲሆን ያደረገችው።

እነዚህ ስብስቦች ግን ከኢትዮጵያ ለመሸሽ የግእዝ/አማርኛን ፊደል በመጤ የላቲን ፊደል የተኩ የማ*ህ*ይ*ም መጨረሻዎች ናቸው። የኦሮምኛ ቋንቋ አህጉር ተሻግሮ በመጣ የላቲን ፊደል እንዲተካ የተደረገው በ1984 ዓ.ም. ነው። ይህን ያደረጉት የግዕዝ/አማርኛ ፊደል የዐማራ ብቻ ስለመሰላቸውና በዐማራ፣ በአማርኛና በግዕዝም ላይ በነበራቸው ጥላቻ የተነሣ ነው።

ዛሬ በአለም ላይ የራሳቸው የሆነ የጽህፈት ስርዓት ወይም ፊደላት አላቸው ከሚባሉት ቻይና፣ ሕንድ፣ ፋርስ፣ ግሪክ፣ ሮም፣ እስራኤል፣ ባቢሎን እና ግብፅ መካከል ኢትዮጵያ አንዷ የሆነችው ግእዝ ከሚናገሩ አግዓዝያን እና አማርኛ ከሚናገሩ ዐማራዎች የተገኘ ነው። የግዕዝ ፊደል የሚባሉት 24ቱ' ፥ሀ፥ ለ፥ ሐ፥ መ፥ ሠ፥ ረ፥ ሰ፥ ቀ፥ በ፥ ተ፥ ኀ፥ ነ፥ አ፥ ከ፥ ወ፥ ዐ፥ ዘ፥ የ፥ ደ፥ ገ፥ ጠ፥ ጸ፥ ፀ፥ ፈ፥ ናቸው። እነዚህ የግዕዝ ፊደል ኆኅያት ለአማርኛ ቋንቋ በቂ ሆኖ ስላልተገኘ የዐማራ የትምህርቱ ኀላፊዎች ከግእዝ ፊደል ተጨማሪ ምልክትና ተጨማሪ ኆኄያትን መፍጠር ስላስፈለጋቸው፣ የኆኄዎች ምንጮች የቶቹ የግዕዝ ኆኄዎች እንደሆኑ አጥንተው ፦
ግዕዝ አማርኛ
ከ “ደ” “ጀ”ን
ከ“ጠ” “ጨ”ን
ከ“ሰ” "ሸ”ን
ከ"ነ" ”ኘ”ን
ከ “ተ” “ቸ” ን
ከ"ከ" "ኸ"ን
ከ"ዘ" "ዠ"ን አስወለዱ።

እነዚህ ሰባት ግንደ ፊደላት ከእንዚሮቻቸው ጋር ሲደመሩ 49 ይሆናሉ። የኢትዮጵያ የፊደላት ቁጥር ከግዕዝ ኆኄዎች 24'ቱ ከግሪኮች ኆኄዎች 2'ቱ ፊደላት ከአማርኛ ኆኄዎች 7' ቱ ፊደላት ተደምረው ወደ 33 ኆኄዎች ሊያድግ ችሏል።

ኢትዮጵያ በነዚህ ፊደላት አማካኝነት ልጆቿን አስተምራለች፣ ለወግ ለማዕረግ አብቅታለች፣ ታሪኳንና ማንነቷን ፅፋበታለች፣ ነገሥታቶቿ እና ደራሲዎቿ አያሌ ጉዳዮችን ፅፈውባቸዋል። የኢትዮጵያ የማንነት ሐውልት የተገነባውና የቆመው በእነዚህ ፊደላት ነው። እንደ አኩስም፣ እንደ ላሊበላ፣ እንደ ጎንደር ኪነ-ሕንፃዎች አባቶቻችን ያወረሱን ድንቅዬ ቅርሶች፣ የማንነታችን መገለጫ ሀብቶች ናቸው።

ነገርግን በአልባኒያ የኮሚኒዝም ፍልስፍና የሰከሩና
የጐሣ ዕፀ ፋርስ ያሳበዳቸው እንደ ኦሮሞ ነፃነት ግንባር ያሉ ቡድኖች የግእዝ/አማርኛ ፊደል አንፈልግም ብለው ባህር ማዶ ተሻግረው የላቲንን አምጥተዋል። በግእዙ በሁለት ፊደል "ቄሮ" ብሎ ከመጻፍ በላቲን 7 ፊደል "Qeerroo" ብለን ነው የምንጽፈው አሉ ይሄው እየደረደሩት ነው።


ማንኛውንም ሀሳብና አስተያየት በዚህ ሊንክ መላክ ይችላሉ @Tadeletibebut
14.8K viewsTadele Tibebu, edited  17:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-06 17:27:42
34.3K viewsTadele Tibebu, 14:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-16 11:25:37
17.7K viewsTadele Tibebu, 08:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-16 11:25:36
17.7K viewsTadele Tibebu, 08:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-16 11:25:18 የድንጋዩ ግዝፈት፣ የመቃብሩ ጥልቀትና የመቃብር ዘበኞች የክርስቶስን ትንሳዔ እንዳላስቀሩት ሁሉ፤ የዐማራን ትንሣኤ እንደ ዔሳው ብርኩናቸውን የሸጡ የይሁዳ ፍየሎች (The Judas goat) ሆኑ፣ የሀገሪቱ ፊልድ ማርሻሎች አያስቀሩትም። እስራኤላውያን ከፈርዖን ባርነት ነፃ ለመውጣት የፈጀውን ያህል ግዜ ይወስድ እንደሆነ እንጂ
እንደ ኡጋንዳው ኢዲ አሚን ዳዳ ያሉ አምባገነኖች የዐማራ ትንሣኤን አያስቀሩትም። እንደ ፕሮፌሰር አሥራት ያሉ ተቆርቋሪ ዐማሮችን ልክ እንደ "ቀያፋ" እንዲያዙ ምክር የሚሰጡ ተላላኪዎች ትንሳኤውን አያስቀሩትም። በኢየሩሳሌም ሊቀ ካህናት የነበረው ቀያፋ እየሱስን ለማስያዝና ፍርድ እንዲፈረድበት፣ "ሕዝብ ሁሉ ከሚጠፋ አንድ ሰው ቢሞት ይሻላል" ብሎ የመከረ ሰው ነው። ምክሩ ግን የክርስቶስን ትንሳኤ አላስቀረውም።

በአንጻሩ፣ ዛሬ ትንሳኤ ላይ ያሉ የሚመስላቸው መጨረሻቸው እንደ አሚን ዳዳ ስደተኛና ፍርደኛ እንደሚሆኑ ምንም ጥርጥር የለም። "ያለምንም ደም፤ ያለምንም ደም" (With out blood, without blood) በሚል መፎክር የተጀመረው የደርግ አብዮት ኢትዮጵያውያንን በመረፍረፍ ከተጠናቀቀ በኋላ፣ ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያም የሞት ጠረን ሸተተኝ ብሎ ፈርጥጦ ዝምባዋብዌ ገብቷል። የደርግን ሥርዓት በቀይ ሽብር በመደዳ ጭፍጨፋ ገድሎ የሸጠው ሬሳ የብረት ዓምድ ሆኖ አላስቆመውም። የዘረፈው ንብረት መሰላል ሆኖ አላቆየውም። ይልቁንስ እንደ በግ እየነዳ ያረደው የደም ጎርፍ ጠራርጎ ወሰደው። በነ ማርክስ ቴዎሪ የረገጠው ሃይማኖት እንጦሮጦስ አወረደው።

ዛሬ ትንሣኤ ላይ ያሉ የሚመስላቸው አምባገነኖች
የዐማራን ህዝብ እንደ ሂትለር፣ ሙሶሎኒ፣ ስታሊን፣ ፓል ፖት እያሰቃዩ፣ እየጨፈጨፉና እያፈናቀሉ መሠረትነው የሚሉት ርዕዮተዓለም እንደ ናዚ ፓርቲ መንኮታኮቱ አይቀርም። ወለጋ ውስጥ አንዲት የ6 ዓመት ህፃን "ወላሂ ሁለተኛ ዐማራ አልሆነም" እያለች በጉንጮቿ ያፈሰሰችው ዕንባ፣ እየተሳለቁ!..ለማየት በሚያሣሣ ገላዋ ላይ እሽቅድምድም በሚመስል መልኩ ባዘነቡት የጥይት አረር ያፈሰሱት ደሟ የእንጦሮጦስን ጎዳና መጥረጉ አይቀርም።

ይህ ታሪክ ከሩዋንዳዋ ህፃን ጋር የሚመሳሰል ነው። ሩዋንዳ ውስጥ በነበረው ፍጅት ወቅት አንዲት የ7 ዓመት ህፃን በሁቱ ገዳዮች ተከባ "እባካችሁ አትግደሉኝ። ከእንግዲህ ቱትሲ አልሆነም" (Please don't kill me, I will never be a Tutsi again) እያለች መማፀኗን ተከትሎ የዓለምን ልብ ሰብረው ነበር። ይህ የሁቱዎች ጭካኔ የተቱሲዎችን ትንሣኤ አላስቀረውም። ቱትሲዎች ሥልጣን ይዘው በደም የታጠበችውን ሩዋንዳን ውብና ፅዱ፣ የቱሪስቶች መዳረሻ፣ ለኢንቨስትመንት ተመራጭ አደረጓት። ከትንሣኤው በኋላ የሩዋንዳ ህፃናቶች በውቧ ኪጋሊ ከተማ መናፈሻዎች ሲቦርቁ ታዩ።

ዛሬም በአዳነች አበቤ የከንቲባነት ዘመን በአዲስአበባ ከተማ ቤታቸው ፈርሶ መጠጊያ አጥተው የሚንከራተቱ፣ በፈረስ ጋሪ ከቤት እቃ ጋር ተጭነው የሚሰደዱ ህፃናቶች ዕንባ በዮዲት ጉዲት የወረደውን አይነት መቅሰፍት ማምጣቱ አይቀርም። ግፈኞች ወደ ከርሠ መቃብርና ወህኒ ሲወርዱ፣ የአዲስአበባ ህፃናቶች፣ የወለጋ ህፃናቶች፣ ተፈናቀለው በመጠለያ ካምፕ የሚገኙ ህፃናቶች የሩዋንዳን አይነት የትንሣኤ ዘመን ይመጣላቸዋል።

የግፈኞች መጨረሻ ግን እንደ መንጌ መፈርጠጥ፤ እንደ ዣን ፖል እስርቤት መሆኑ አይቀርም። የሩዋንዳዋ ታባ ከተማ ከንቲባ የነበረው "ዣን ፖል አካይሱ" በፈፀመው የዘር ጭፍጨፋና ሰብዓዊ መብት ጥሰት ከፍርድ እንዳላመለጠው ሁሉ፣ አዲስአበባ ላይ እንደ ዣን ፖል ግፍ እየፈጸሙ ያሉ ሰዎች ዕጣ ፈንታ እንደ ዣን ፖል ይሆናል። በወቅቱ ባንኩና ታንኩ በእጃችን ነው ብለው በጥጋባቸው ቦሲኒያን የጨፈጨፉት ጄነራል ራዲስላቭ ክርስቲች እና ኮማንደር ራትኮ ምላዲች ከፍርድ አላመለጡም። ስለዚህ ግፈኞች ሲዋረዱ እንጂ ትንሳኤን አስቀርተው አያውቁም። ናዚዎች በኑምበርግ ፍርድቤት ቀርበው የዕድሜ ልክና የስቅላት ቅጣታቸውን አገኙ እንጂ፣ የእስራኤላውያንን ትንሳኤ አላስቀሩትም። ሁቱዎች በወረንጦ እየተለቀሙ ፍርዳቸውን አገኙ እንጂ የቱትሲዎችን ትንሣኤ አላስቀሩትም። ኢትዮጵያ ላይ ይህ ዘመን አይርቅም።

ከስቅለት በኋሏ ትንሳኤ፤ ከጨለማ በኋላም ብርሀን አለና!
17.6K viewsTadele Tibebu, edited  08:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 16:19:43
27.6K viewsTadele Tibebu, 13:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 16:19:11 እንኳን ለጽሎተ ሐሙስ በሰላም አደረሳችሁ!
ጸሎተ ሐሙስ ጌታችን ምሥጢረ ቊርባንን ከምሥጢረ ጸሎት ጋር አዋሕዶ የገለጠበት ዕለት ነው። ትህትና!
25.4K viewsTadele Tibebu, 13:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 10:26:56
29.1K viewsTadele Tibebu, 07:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 14:03:49
15.4K viewsTadele Tibebu, 11:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ