Get Mystery Box with random crypto!

Skyline media

የቴሌግራም ቻናል አርማ skyline7777 — Skyline media S
የቴሌግራም ቻናል አርማ skyline7777 — Skyline media
የሰርጥ አድራሻ: @skyline7777
ምድቦች: መኪናዎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 50.78K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የኢትዮ ስካይላይን የቴሌግራም ቻናል ነው። 🙌 ዓላማችን እናንተን ውድ ተከታታዮቻችንን በቅድሚያ ማሳወቅ ፣ ማስተማርና ዘና ፈታ የሚያደርጉ ርዕሰ ጉዳዩች ላይ በማተኮር ማገልገል ነው 🙌
ቁም ነገሮች፣ ቀልዶች፣fun GIF:ትረካዎች:
መጣጥፎች ሌሎችንም ዜናዎች የሚያገኙበት ምርጥ ቻናል🤗
ለጥቆማና አስተያየታችሁ
For any promotion 👉 @Skyline7777

Ratings & Reviews

5.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

3

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-07-23 16:32:39
ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በሮም እየተካሄደ ባለው የልማት እና የፍልሰት ኮንፈረንስ ላይ እየተሳተፉ ነው

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 16፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በጣልያን ሮም እየተካሄደ በሚገኘው ዓለም አቀፍ የልማት እና የፍልሰት ኮንፈረንስ ላይ እየተሳተፉ ነው።

ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ካላት ስትራቴጂካዊ አቅም አንጻር የስደት ምንጭ መሸጋገሪያ እና መድረሻ መሆኗ ተገልጿል።

በዚህም መሠረት ኢትዮጵያ የስደት አስተዳደርን ለማጎልበት፣ ሕገ ወጥ ስደትን እና ሕገ ወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመፍታት በርካታ የፖሊሲ፣ የሕግ እና ተቋማዊ እርምጃዎችን መወሰዷን ከጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
2.6K viewsAnt B, 13:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-23 04:22:26 Channel name was changed to «Skyline media»
01:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-23 04:22:25 Channel photo updated
01:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-18 22:02:36 https://fb.watch/lSCQXLPVHa/?mibextid=6aamW6
6.0K viewsAnt B, 19:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-15 22:07:17 ዜና ሹመት
የፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ለተለያዮ የስራ ሃላፊዎች ሹመት ሰጠ፡፡
›››››››››››››››››››››››››››››››››››››››››››
ጉባኤው ዛሬ ሃምሌ 05 ቀን 2015 ዓ.ም ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚደንት አቅራቢነት ለቀረቡ ለተለያዮ የስራ ሃላፊዎች ሹመት ሰጥቷል፡፡በዚህም መሰረት
1ኛ) አቶ አንቢኮ ጃርሳን የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ኮርት ማናጀር
2ኛ) አቶ ኡቦንግ ኡጁሉ ጊሎን የጠቅላይ ፍርድ ቤት የጉዳዮች ፍሰት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር
3ኛ) አቶ አጃማ ጋዲሳን የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ኢንስፔክሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አድርጎ ሾሟል፡፡
በሌላ በኩል በአንድ ረዳት ዳኛ ላይ በቀረበ የዲሲፕሊን ጉዳይ ላይ ተወያይቶ የአንድ ወር ደመወዝ እንዲቀጡ ወስኗል፡፡
የፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ጽ/ቤትም አዲስ ለተሾሙት የስራ ሃላፊዎች መልካም የስራ ዘመን እንዲሆንላችሁ ይመኛል::
8.1K viewsAnt B, 19:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-15 14:09:29
የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ "በቅርቡ" በኢትዮጵያ ጉብኝት እንደሚያደርጉ የጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ የብሄራዊ ደኅንነት አማካሪ ሬድዋን ሁሴን በትዊተር ገጻቸው አስታውቀዋል።

ዶር ዐቢይና ፕ/ር ኢሳያስ ካይሮ ላይ በኹለትዮሽ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ማድረጋቸውን የጠቀሱት አቶ ሬድዋን፣ ፕ/ር ኢሳያስ በቅርቡ በኢትዮጵያ በሚያደርጉት ጉብኝት ተጨማሪ ውይይት ለማድረግ እንደተስማሙ ገልጸዋል።

ፕ/ር ኢሳያስ ጉብኝቱን ካካሄዱ፣ በኢትዮጵያ መንግሥትና ሕወሃት መካከል የግጭት ማቆም ስምምነቱ ከተፈረመ ወዲህ ጉብኝቱ የመጀመሪያቸው ይኾናል።
7.7K viewsAnt B, 11:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-14 11:05:51
አባ ሰረቀ በቦሌ ኤርፖርት እንዲህ ቁጭ ብለዋል። አድረዋል።
ወደመጡበት አውስትራሊያ እንዲመለሱ ተነግሯቸዋል። አልታሰሩም።
ኤጶስ ቆጶሳትን በህገወጥ መንገድ ያለ ቤተክርስቲያን ቀኖና ለመሾም ወደ ትግራይ ለመሄድ ቢፈልጉ ተከልክለዋል።
አባ ሰረቀ ኢትዮጵያ ጋለሞታ ነች፣ ኢትዮጵያ ኤልዛቤል ነች እያሉ ሀገርን ሲሳደቡ እንደነበረ ይታወሳል።
አማራንም እንዲሁ እንደ ህዝብ ሲሳደቡ ነበረ።
ወደ ኢትዮጵያ የመጡት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶን ለመክፈል ተልዕኮ ይዘው ነው።
6.6K viewsAnt B, 08:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-12 12:17:45
ባንኮች በግድ ቦንድ እንዲገዙ ተገደዋል ይላል ሪፖርተር። በዚህም 25ቢ ብር መንግስት ሰብስቧል
6.3K viewsAnt B, 09:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-10 00:13:12
ለአዲስ አበባ ከተማ 140.2 ቢሊዮን ብር ጸደቀ

የአዲስ አበባ ከተማ የ2016 በጀት 140.29 ቢሊዮን ብር ሆኖ በከተማዋ ምክር ቤት ጸደቀ፡፡ በዘንድሮው የ2016 በጀት ዓመት ለከተማ አስተዳደሩ የተያዘው በጀት ካለፈው በጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ40.2 ቢሊዮን ብር ብልጫ አለው፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የከተማዋን በጀት ያጸደቀው ዛሬ እሁድ ሐምሌ 2፤ 2015 ለሁለተኛ ቀን ባካሄደው መደበኛ ስብሰባው ነው፡፡ በዛሬው የምክር ቤቱ ውሎ ትላንት ለተጀመረው የ2016 በጀት ዓመት የሚውል የበጀት ዝርዝር የያዘ አዋጅ ለምክር ቤት አባላቱ ቀርቧል፡፡ የከተማ ምክር ቤቱ በበጀት አዋጁ ላይ ውይይት ካደረገ በኋላ በ87 ድጋፍ እና በሁለት ድምጸ ተዐቅቦ በአብላጫ ድምጽ የ2016ን በጀት ጸድቋል፡፡

በአዲሱ በጀት ዓመት ለአዲስ አበባ ከተማ የተያዘውን በጀት ዝርዝር የተያያዘውን ቪዲዮ ተጭነው ይመልከቱ፡፡

@EthiopianInsider1
7.0K viewsAnt B, 21:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-09 22:21:25 ለExit Exam ተፈታኝ ተማሪዎች በሙሉ
ትምህርት ሚኒስቴር በሀገሪቱ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ተግባራዊ ማድረግ ከጀመራቸው ስራዎች አንዱ የሆነ የተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ከነገ ሐምሌ 3 ቀን 2015 ዓ/ም ይጀምራል።

በዚህ ፈተና ወቅት ከተማሪዎች እና ከፈታኞች ምን እጠበቃል ?

[ ከተፈታኞች የሚጠበቅ ]

- ተፈታኞች ወደ መፈተኛ ክፍል ሲመጡ ማንኛውም አይነት ስልክ፣ ስማርት ሰዓት ፣ ታብሌት ፣ ላፕቶፕና ... ወዘተ ተመሳሳይ ኤክትሮኒክ ቁሳቁስ መያዝ በፍፁም የተከለከለ ነው።  (ይዞ የተገኘ ፈተናው /ውጤቱ ተሰርዞበት በቀጣይ ጊዜ እንዲቀመጥ ይደርጋል)

- ፈተና ከመጀመሩ ከ30 ደቂቃ በፊት መፈተኛ ክፍል መገኘት አለባቸው ይህም ማለት ከጥዋቱ 2፡00 በፊት ፤ ከሰዓት ደግሞ ከ8፡00 በፊት ተፈታኞች መገኘት አለባቸው።

- ተፈታኞች ለፈተና ሲመጡ ID መያዝ ያለባቸው ሲሆን User Name እና Password lower-case and upper-case ፊደላትን ለይተው በጥንቃቄ መያዝ አለባቸው።

- ተፈታኞች ፈተና ከተጀመረ በኃላ ከ30 ደቂቃ በፊት ከፈተናው ክፍል መውጣት የለባቸውም።

- ተፈታኞች ፤ ፈተናውን የሚያስፈትኑ መምህራን በሚያሳዩት ቦታ ብቻ መቀመጥ አለባቸው።

- ሁሉም ተፈታኝ እንዲቀመጥ የተመደበበት የራሱ ኮምፒውተር ላይ ብቻ ተቀምጦ መክፈትና መጠቀም አለበት።

- በፈተና ክፍል ውስጥ መነጋገር እና ከቦታ ቦታ መዘዋወር በፍፁም የተከለከለ ነው። እንዲሁም ማንኛውም ተፈታኝ ከጎኑ ያለውን ተማሪ ኮምፒውተር በፍፁም ማየት የለበትም።

- ምንም ዓይነት ወረቀት ወደ መፈተኛ ክፍል ይዞ መምጣት አይቻልም።

- ተፈታኞች በምንም አይነት ሁኔታ መኮርጅም ሆነ ማስኮርጅ ተግባር ላይ ቢሳተፉ እርምጃ ይወሰድባቸዋል።

- ሁሉም ተፈታኞች ለፈታኝ መምህራን እንዲሁም ለአስተባባሪዎች መታዘዝ ያለባቸው ሲሆን የፈተናው ደንብ እና ስርዓት ተገዢ መሆን ይጠበቅባቸዋል።

NB. ሁሉም ተፈታኞች ወደ ፈተና መፈኛ ክፍል ተፈትሸው እንዲገቡ የሚደረግ ሲሆን ማንኛውም ተፈታኝ ከፀጥታ ኃይሉ ጋር በፍተሻ ወቅት ይሁን ሥርዓት ለማስያዝ በሚደረግ እንቅስቃሴ እንቅፋት ሆኖ ከተገኘ ከመፈተኛ አከባቢ እንዲገለል ተደርጎ በቀጣዩ የመውጫ ፈተና መስጫ ወቅት እንዲቀመጥ ይፈቀድለታል።

[ ከፈታኝ መምህራን የሚጠበቅ ]

- የተፈታኝ ተማሪዎችን ID በአግባቡ በማረጋገጥ ወደ ክፍል እንዲገቡ ማደረግ ይጠበቅባቸዋል።

- ተፈታኝ ተማሪዎችን በሥም ዝርዝራቸው መሠረት ማስቀመጥ ይኖርባቸዋል።

- ፈታኝ መምራህን የተፈታኝ ተማሪዎችን አቴንዳንሰ ይወስዳሉ ፤ ተማሪዎችን ፊርማ ያስፈርማሉ።

- በፈተና ክፍል ውስጥ ደምጽ እንዳይሰማ፣ ተማሪዎች ከቦታ ቦታ እንዳይዘዋወሩ ተገቢውን ቁጥጥር ማድረግ አለባቸው።

- የፈተናው አጠቃለይ ሂደት በትኩረት መከታተል አለባቸው።

- በህመም ምክንያት ተማሪዎች ከመተኛ ክፍል መውጣት ቢፈልጉ ከሱፐርቨዘር ጋር በመነጋገር አስፈላጊውን እርዳታ ያደርጋሉ።

- ተማሪዎች በጎናቸው ያለውን ሌላ ኮምፒውተር እንዳይመለከቱ መቆጣጠር አለባቸው።

- ተማሪዎች ፈተናው ከተጀመረ ከ30 ደቂቃ በፊት እንዳይወጡ መቆጣጠር ይጠበቅባቸዋል።

- ሲኮርጅ ወይም ሲያስኮርጅ የተገኘ ማንኛውም ተማሪ ከመፈተኛ ክፍል እንዲወጣ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።

- ፈተናው ከጀመረ 15 ደቂቃ በኃላ የሚመጣ ተማሪ እንዲገባ ማድረግ የላባቸውም።
- የፈተና አፈጻጸም ሪፖርት ለሱፐርቨዘር ማቅረብ ይጠብቅባቸዋል።
5.7K viewsAnt B, 19:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ