Get Mystery Box with random crypto!

የሣውላ ከተማ አስተዳደር ፤ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ዕውቅና ውጭ የሚንቀሳቀሱ | Natnael Mekonnen

የሣውላ ከተማ አስተዳደር ፤ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ዕውቅና ውጭ የሚንቀሳቀሱ አካላትን " አላስተናግድም " አለ።

" የመንግሥት ተቀዳሚ ተግባር የአከባቢውንና የህዝቡን ሠላም ማስጠበቅ ነው " ያለው የከተማው አስተዳደር ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ዕውቅና ውጭ የሚንቀሳቀሱ አካላትን ከተማዋ ተቀብላ አታስተናግድም ብሏል።

የሣውላ ከተማ ከንቲባ አቶ ሙሉቀን ጉጃ ፤ " የደንባ ጎፋ ወረዳ ቤተክህነት በህገወጥ መንገድ ጳጳሳት የሆኑ አካላት ወደ አካባቢያችን እየተንቀሳቀሱ መሆኑን መረጃው ደርሶኛል ሲል በፃፈው ደብዳቤ ገልፆልን መንግስትና የፀጥታ አካላት ቅድስት ቤተክርስቲያንና የአካባቢውን ሠላም በቅርበት እንዲከታተልና የህግ የበላይነት እንዲረጋገጥ ጠይቀናል " ሲሉ ተናግረዋል።

ከንቲባው ፤ ህብረተሰቡ የሠላም ማስከበር ስራውን አጠናክሮ እንዲያስቀጥል፤ በአከባቢው እንግዳ ነገሮች ሲያጋጥሙ ጥቆማ እንዲሰጥና ከፀጥታ አካላት ጎን በመሆን የተለመደ ተግባሩን እንዲያከናውን ጥሪ አቅርበዋል።

በተጨማሪ ህዝበ ክርስቲያኑ ያለአንዳች የፀጥታ ስጋት በፆመ ነነዌ የጀመረውን ሱባኤ በአርምሞ እንዲያከናውን በመግለፅ የከተማው መንግሥት ከፖሊስ እንዲሁም ከሠላምና ፀጥታ መዋቅሮች ጋር በጋራ በመቀናጀት የአከባቢውን ደህንነት እንደሚያስጠብቁ አረጋግጠዋል።

በከተማዋ ላሉ አቢያተ ክርስቲያናት መንግሰት የተጠናከረ ጥበቃ እንደሚያደርግ ከንቲባው አሳውቀዋል።