Get Mystery Box with random crypto!

Muktarovich Ousmanova

የሰርጥ አድራሻ: @muktarovichousmanova
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 63.90K
የሰርጥ መግለጫ

Ethiopia forever

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2024-04-21 13:33:04
➷አስገራሚው መንደር በፍጹም እንዳያመልጣችሁ!!!
ጊዮን ሆምስ የጊዮን ቢዝነስ ግሩፕ አካል
+251921388158
በመሃል ከተማ ሌላ ከተማ እየገነባ ይገኛል።
➷ወሎ ሰፈር መስቀል ፍላወር አጠገብ
50%የባንክ ብድር የተመቻቸለት
90% የተገነባ መንደር አፓርትመንቶች
በ10 % ቅድመ ክፍያ ብቻ የቤት ባለቤት
ይሁኑ
ባለ 1,መኝታ ➷96.5ካሬ
ባለ 2 መኝታ ➷168.9ካሬ
➷144ካሬ
ባለ 3 መኝታ 205ካሬ
ባለ 4 መኝታ 215ካሬ
➷50 አመት በቢዝነሱ ዘርፍ ልምድ ያካበተው
በውስጡ ስምንት እህት ኩባንያዎችን የያዘ
ጊዮን ቢዝነስ ግሩፕ
https://youtube.com/@Modernhouseinethiopia?si=O1OgP4AI7Re2Yv5w
15.7K views10:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-21 12:49:50
ቀሲስ በላይ ዶላር ለማጭበርበር የሞከሩት ከአፍሪካ ህብረት አካውንት ነው

" ቀሲስ በላይ በአፍሪካ ህብረት ቅጥር ጊቢ ዉስጥ በሚገኝ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ በመገኘት ሀሰተኛ ሰነድ በመጠቀም ከህብረቱ የሂሳብ ቁጥር ለግንባታ እና ሌሎች ስራዎች ክፍያ በሚል 6 ሚሊዮን 50 ሺህ ዶላር ለማዘዋወር ሲሞክሩ በቁጥጥር ስር ዉለዋል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ በአፍሪካ ህብረት ቅጥር ጊቢ ዉስጥ ያለዉ ቅርንጫፉ ከሁለት አስርት ዓመታት በፊት የተከፈተ ሲሆን በዋነኛነት የአፍሪካ ሒሳቦችን በተለይ ለማስተዳደር ነው። ከዚያን ጊዜ ጀምሮም የአፍሪካ የበሽታ መቆጣጠሪያ ማዕከልን ጨምሮ የተቋሙ ከፍተኛ የዉጭ ምንዛሪ ክምችት ያላቸዉ አካውንቶችን በማካተት ቁጥጥር ያደርጋል።

ቀሲስ በላይ በወቅቱ ሀሰተኛ የህብረቱ ማህተም ያረፈባቸዉን ወረቀቶች በመያዝ ለግንባታ እና የማሽነሪዎች አቅርቦት በሚል ክፍያዉን መጠየቃቸውን ሪፖርተር ዘግቧል።

ክፍያዉ ከመፈጸሙ በፊት ወደ ህብረቱ የስልክ ጥሪ ያደረጉት የባንኩ ሰራኞች የክፍያዉን ትክክለኛነት ለማረጋገጥ ሲሞክሩ የህብረቱ የፋይናንስ ክፍል የማያዉቀዉ መሆኑን እና ክፍያዉ እንዲታገድ ህብረቱ መጠየቁ መረጃዉ ይደርሳቸዋል።

ህብረቱ ይህንን ተከትሎም ግለሰቡ እንዲያዙለት ጠይቆ ቀሲስ በላይ በህብረቱ ጠባቂዎች በቁጥጥር ስር ዉለዉ በፌዴራል ፖሊስ ተላልፈው መሰጠታቸዉ ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቤ ሳኖ እንደተናገሩት "በመሠረቱ ጥሬ ገንዘብ በውጭ ምንዛሪ ብቻ ሊሰጥ አይችልም ። ለማጭበርበር የሞከረዉም ግለሰብ መጥቶ መጠኑን በጥሬ ገንዘብ ሲጠይቅ ይህን እንኳን አያውቅም ነበር ማለታቸዉን ነዉ።


ሪፖርተር
16.0K views09:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-19 19:56:05
የቡድን ሰባት ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በኢትዮጵያ በርካታ አካባቢዎች ይታያሉ ያሏቸው፤ “የማያቋርጡ እና ኃይለኛ ውጥረቶች” እንደሚያሳስቧቸው ገለጹ። በኢንዱስትሪ የበለጸጉት ሰባት አገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በኢትዮጵያ ይፈጸማሉ የሚባሉ “የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች እና በደሎች ሪፖርቶች”፣ “ብርቱ ኢኮኖሚያዊ ቀውስ” እና “የምግብ ዋስትና እጦት መስፋፋት” እንዳሰጋቸውም አስታውቀዋል።

ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮቹ በኢትዮጵያ ጉዳይ ስጋታቸውን ያንጸባረቁት፤ በጣልያኗ ካፕሪ ደሴት ያካሄዱትን ስብሰባ ሲያጠናቅቁ ዛሬ አርብ ምሽት ባወጡት መግለጫ ነው። ሚኒስትሮቹ በዚሁ መግለጫቸው፤ በኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት እና በህወሓት መካከል በተፈረመው ግጭት የማቆም ስምምነት አተገባበር ረገድ የተወሰዱ እርምጃዎችን በበጎ እንደሚቀበሉ ገልጸዋል።

በሰብዓዊ መብቶች እና በሲቪል ሰዎች ጥበቃ፣ ውጥረቶችን ለመፍታት በሚደረግ ፖለቲካዊ ውይይት፣ በዕርቅ፣ በብሔራዊ ውይይት፣ የሽግግር ፍትህ እና በግጭት ወቅት ወንጀል የፈጸሙ ተጠያቂ ለማድረግ ተጨማሪ እና ዘላቂ እርምጃዎች ተግባራዊ እንዲደረጉ አበረታተዋል። በሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎች በመካሄድ ላይ በሚገኙ ግጭቶች የሚሳተፉ ወገኖች፤ በንግግር ሰላም ለማውረድ ተመሳሳይ ቁርጠኝነት እንዲኖራቸው ጥሪ አቅርበዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
14.1K views16:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-19 14:19:03
የአንድ አመት ልጁን ከእነ ህይወቷ ለመቅበር የሞከረው ወላጅ አባት በቁጥጥር ስር ዋለ።
#FastMereja
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በቤንች ሸኮ ዞን የሰሜን ቤንች ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ረዳት ኢንስፒክተር አለማየሁ አማረ ለክልሉ ፖሊስ የህዝብ ግንኙነትና ኮሚንኬሽን እንደገለፁት በወረዳው ኮሶል ቀጭን መንደር ሚያዚያ 10 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 11:00 ሰዓት ላይ በባልና ሚስት መካከል በተፈጠረው ፀብ ምክንያት የወንጀል ድርጊቱን ለመፈፀም ሙከራ ማድረጉን አስረድተዋል፡፡

አዛዡ አክለውም በባልና ሚስት መካከል በተፈጠረ ጊዜያዊ ፀብ እናት የአንድ ዓመት ሴት ህፃን ልጅ ጥላ በመጥፋቷ ወላጅ አባት ቲቲዮስ ኪያግላስ የተባለው ተጠርጣሪ የአንድ ዓመት ህፃን ልጁ እያለቀሰች ስታስቸግረዉ በሁኔታው ተበሳጭቶ የአንድ አመት ልጁን በህይወት ለመቅበር ጉድጓድ ሲያዘጋጅ የተመለከቱ የአከባቢው ነዋሪዎች ለፖሊስ ጥቆማ ይሰጣሉ፡፡

ፖሊስ በደረሰው ጥቆማ መሰረት ተጠርጣሪውን ጉድጓድ እየቆፈረ እያለ በቁጥጥር ስር እንዲውል በማድረግ ህፃኗን ጉዳት ሳይደርስባት መታደግ መቻሉንና በተጠርጣሪው ላይ ምርመራ እየተጣራበት እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡

ፖሊስ የህፃኗን ወላጅ እናቷን እያፈላለገ ሲሆን ህፃኗ በአሁን ሰዓት ሰሜን ቤንች ወረዳ ፖሊስ እንክብካቤ እያደረገላት እንደሚገኝ የገለፀት ፖሊስ አዛዡ በቤተሰብ መካካል አለመግባባቶች በሚፈጠሩበት ወቅት ችግሩን በመነጋገር መፍታት ይገባል ሲሉ ፖሊስ አዛዡ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ሲል ፋስት መረጃ ከክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነትና ኮሚንኬሽን መረጃ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
16.5K views11:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-19 07:29:24
ስልክዎትን ለመቀየር ወይም አዲስ ለመግዛት አስበዋል ?

አዳዲስ እንዲሁም በመጠኑ ያገለገሉ ስልኮችን ከተሟላ ዋስትና እና ጥገና ጋር ይዘን ቀርበናል ለበለጠ መረጃ ቻናላችንን ይጎበኙ

https://t.me/sellphone2777

0929008292

inbox @bina27

አድራሻ- ቦሌ ከሸገር ህንፃ አጠገብ

ክፍለ ሀገር ላላቸሁ ደንበኞችቻችንም በ DHL መላክ ጀምረናል
17.0K views04:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-19 07:02:45
ትናንት ማታ በኬንያ መርሳቤት አከባቢ በደረሰ የጄሎኮፍተር አደጋ የኬንያ የመከላከያ አዛዥ ፍራንሲስ ኦጎላን ጨምሮ በርካታ የወታደራዊ አዛዦች መሞታቸው ተገለፀ
16.6K views04:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-18 14:32:31
በብራዚል በሞተ ሰው ስም ብድር ለመውሰድ አስክሬኑን በዊልቸር ላይ አድርጋ ወደ ባንክ የመጣችዉ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለች

የ42 ዓመቷ ብራዚላዊት ሴት ህይወቱ ያለፈ ባለቤቷን ወደ ባንክ አምጥታ በስሙ ከባንክ ብድር ለማዉጣት ስትሞክር በቅርቡ በቁጥጥር ስር ውላለች።

ማክሰኞ ሚያዚያ 9 ቀን ኤሪካ ዴ ሱዛ ቪየራ ኑነስ የተባለችዉ ግለሰብ ህይወቱ ካለፈዉ የ68 ዓመቱ ፓውሎ ሮቤርቶ ብራጋ ስም 3,200 ዶላር የባንክ ብድር ለማዉጣት ወደ ባንጉ፣ ሪዮ ዴጄኔሮ ወደሚገኘው የኢታው ዩኒ ባንኮ ቅርንጫፍ መጥታለች። የአዛውንቱን በዊልቸር ላይ የነበሩ ሲሆን አጎቷ እንደሆኑ እና የመጀመሪያ ተንከባካቢ መሆኗን ተናግራለች። የባንኩ ሰራተኞች ብዙም ሳይቆይ በብራጋ ላይ ከባድ ችግር እንዳለ አስተውለዋል፡፡ምክንያቱም ይህችዉ ሴት የሟችን ጭንቅላት በእጇ ስትደግፍ ጥርጣሬ ፈጥሮባቸዋል። እናም ምንም አይነት በህይወት እንዳለ የሚያሳይ ምልክት አልታየበትም፣ ነገር ግን ቪየራ ኑነስ በተፈጥሮው ዝምተኛ እንደሆነ ለባንኩ ሰራተኞቹ እየነገራቻቸዉ ነበር ተብሏል።

ምንም እንኳን ለምትጠይቀዉ ጥያቄ መልስ የመስጠት አቅም እንደሌለው ግልጽ ቢሆንም አስክሬኑን ልታናግረው ስትሞክር ትታያለች፡፡“አጎቴ እየሰማህ ነው? መፈረም አለብህ። ካልፈረምክ ምንም መንገድ የለም ” እያለች ስትናገር እንደነበር ምስክሮች ኤሪካ ዴ ሱዛ ቪዬራ ኑነስ በዊልቸር ላይ ለተቀመጠዉ አስከሬን ስትናገር ሰምተዋል፡ "ላንተ መፈረም አልችልም፤ማድረግ የምችለውን አደርጋለሁ፤ ተጨማሪ ራስ ምታት እንዳትሰጠኝ ስምህን መዝግብ ስትል ትደመጣለች፡፡

ከባንኩ ሰራተኞች አንዱ "ደህና ነው ብዬ አላምንም" ሲል ይደመጣል፤ቪዬራ ኑኔስ ግን "አጎቷ" ደህና እንደሆነ ትናገራለች ፣ ትንሽ ዝምታ ስለሚያበዛ ነዉ በማለት ለማስተባበል ሞክራለች፡፡

ዳጉ ጆርናል
18.6K views11:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-18 13:10:29
ቀሲስ በላይ መኮንን በተጠረጠሩበት በሀሰተኛ ሰነድ የዶላር ዝውውር ወንጀል ለምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ቀጠሮ ተፈቀደ
የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀሲስ በላይ መኮንን በተጠረጠሩበት በሀሰተኛ ሰነድ የዶላር ዝውውር ወንጀል ለምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ቀጠሮ ፈቀደ፡፡

የፌደራል ፖሊስ መርማሪ ቀሲስ በላይ መኮንን ከትናንት በስቲያ በአፍሪካ ህብረት ቅጥር ጊቢ ውስጥ በሚገኘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ውስጥ በአካል ቀርበው ሀሰተኛ የክፍያ ሰነዶችን በመያዝ ለ3 ግለሰቦች እና ለአንድ የግል ድርጅት ሒሳብ 6 ሚሊየን 50 ሺህ ዶላር ሊያዘዋውሩ ሲሉ በአፍሪካ ህብረት ሴኪዩሪቲዎች ተይዘው ለፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ተላልፈው መሰጠታቸውን ጠቅሶ የጥርጣሬ መነሻውን ለችሎቱ አቅርቧል።

በዚህ መነሻ መሰረትም መርማሪ ፖሊስ ተጨማሪ የምርመራ ማጣሪያ ሥራ ለማከናወን የ14 ቀን ጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጠው ጠይቋል።

ተጠርጣሪ ቀሲስ በላይ መኮንን ድርጊቱ መፈጸሙን አምነው፤ ይሁን እንጂ ወንጀል አለመፈጸማቸውን አስረድተዋል፡፡

ስለሆነም የዋስትና መብታቸው እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል።

የግራ ቀኝ ክርክሩን የተመለከተው ጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ተጠርጣሪው ያቀረቡትን የዋስትና ጥያቄ በማለፍ ለፖሊስ የ7 ቀናት የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ፈቅዷል።
#FBC
19.1K views10:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-17 13:19:04
" "የአማራ ታጣቂዎች" ያቋቋሟቸውን አስተዳደሮች ለማፍረስ ከፌደራል መንግስት ጋር ተስማምተናል ሲል የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር አስታወቀ

ይህን ዜና በሰማን በማግስቱ ዛሬ የአማራ ክልል መንግስት ተወረርኩኝ መግለጫ አውጥቷል። የሚገርመው የፌዴራል መንግስት ይህን ወረራ ይከላከልልኝ ማለቱ ነው። ለአለማቀፍ ማህበረሰብም አቤቱታ አሰምቷል። ለአማራ ህዝብና ፋኖም እንደቀድሞው ሁሉ "ሀገርን ከመፍረስ" አብረን በመታገል፣ ከ"ሀዲውን ህወሓት አብረን እንታገል ብሏል
18.7K viewsedited  10:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-16 13:56:48
በከፋ ዞን በገጠመ የትራፊክ አደጋ አምስት ሰው ወዲያው ሲሞት፣ በርካቶች ቀላልና ከባድ የአካል ጉዳት ገጥማቸዋል
20.6K views10:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ