2024-03-27 09:00:26
ላይመለስ ሄዷል | #ነፍስ_ኄር
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን እና የባህርዳር ከተማ አማካይ ስፍራ ተጫዋች የሆነው አለልኝ አዘነ ድንገተኛ ህልፈተ ህይወት ተሰምቷል ።
ለአርባምንጭ ታዳጊ ቡድን እስከ ዋናው ፤ ለሀዋሳ ከተማና ህይወቱ እስካለፈበት ጊዜ ድረስ ለባህርዳር ከተማ በሊጉ የሚጫወተው አለልኝ አዘነ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንም ጥሪ ተደርጎለት አገልግሎቱን ሰጥቷል ።
በቅርቡ በቅድስት ቤተክርስቲያን ስርአተ-ጋብቻዉን የፈፀመው ተጨዋቹ በጉዳት ምክንያት ከክለቡ ስብስብ ጋር ያልነበረ ሲሆን በትዉልድ ቦታው አርባምንጭ መጋቢት 18/2016 ዓ.ም ንጋት ላይ ህልፈተ ህይወቱ ተሰምቷል ።
የቀብር ስነስርዓቱም በዛሬው ዕለት በአርባ ምንጭ ከተማ እንደሚፈፀም ታዉቋል ። ለቤተሰቦቹ ፣ ለቡድን አጋሮቹ ፣ ለአድናቂዎቹ እንዲሁም ለመላው የስፖርት አፍቃሪ መፅናናቱን ይስጥልን ።
[ አሟሟቱን በተመለከተ የተለያዩ መረጃዎች እየወጡ ሲሆን '' #ራሱን_አጠፋ '' የሚለዉ ከሚወጡት መረጃዎች አንዱ እና ዋነኛው ነው ]
16.9K views06:00