Get Mystery Box with random crypto!

Muktarovich Ousmanova

የቴሌግራም ቻናል አርማ muktarovichousmanova — Muktarovich Ousmanova
ርዕሶች ከሰርጥ:
Wazemaalert
Ebc
Pmoethiopia
Westandwithendf
Londonmarathon
Berlinmarathon
Inbox
Fastmereja
Ethiopia
Southafrica
All tags
የሰርጥ አድራሻ: @muktarovichousmanova
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 72.83K
የሰርጥ መግለጫ

Ethiopia forever

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2023-04-14 21:19:00
በአልን ምክንያት በማድርግ

➨ ከ 25 - 35% ቅናሽ በእያንዳንዱ አፓርታማዎች ላይ

  የካሬ አማራጮች፦

          107 ካሬ
          110 ካሬ
          115 ካሬ
          120 ካሬ
          127 ካሬ
          138 ካሬ
          145 ካሬ
          161 ካሬ

በተጨማሪ 145 ካሬ G+1

ቤት በአገር ቤት ከአያት

መልካም ትንሳኤ

@Tsion_won

https://t.me/nvhfjnfdhnojbfedgjn

ለበለጠ መረጃ (Whatsapp/direct)፦ በ 0904444670 ወይም 0912287354 ይደውሉ
13.2K views18:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 21:18:16
ኢትዮጵያ ከአይኤምኤፍ ኹለት ቢሊዮን ዶላር ብድር ትሻለች

በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም መሠረት፣ ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት/አይኤምኤፍ/፣ ኹለት ቢሊዮን ዶላር ብድር ለማግኘት በመወያየት ላይ እንደኾነች፣ ሮይተርስ የተቋሙን ምንጮች ጠቅሶ ዘግቧል።

ከውይይቱ ምስጢራዊነት የተነሣ ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ አራት የሮይተርስ ምንጮች፣ ዋሽንግተን ዲሲ ላይ የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት እና የተቋሙ ሓላፊዎች እያደረጉ በሚገኙት ውይይት፣ አይኤምኤፍ የኢትዮጵያን የመበደር ዐቅም እየገመገመ መኾኑን ተናግረዋል።

በተቋሙ ግምገማ፣ እአአ እስከ 2026 ባለው ጊዜ ውስጥ፣ ኢትዮጵያ ቢያንስ ስድስት ቢሊዮን ዶላር ያህል የገንዘብ እጥረት ሊገጥማት እንደሚችል፣ ለውይይቱ ቅርበት ያላቸው ኹለት ምንጮች ለሮይተርስ ገልጸዋል፡፡ አሁን በግምገማ ላይ ያለው የብድር ጥያቄ ቢሳካላት እንኳ፣ ኢትዮጵያ አራት ቢሊዮን ዶላር እጥረት ሊያጋጥማት እንደሚችል፣ ቅድመ ትንበያ ተቀምጧል።
12.7K views18:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 17:40:00
በኬንያ ክርስቶስን ቶሎ ለማግኘት በረሃብ አድማ ላይ የነበሩ አራት ሰዎች ህይወታቸው አለፈ

በኬንያ የባህር ጠረፍ ኪሊፊ አውራጃ አራት ሰዎች ህይወታቸው አልፈው የተገኙ ሲሆን በርካቶች ደግሞ ክፉኛ መጎዳታቸው የተሰማ ሲሆን የምግብ አድማ በማድረግ የዓለምን ፍጻሜ ሲጠባበቁ እንደነበረ ተጠቁመሟማ። ፖሊስ እንዳስታወቀው ለተከታታይ ቀናት ባጫካ ውስጥ ግለሰቦቹ በፃም "ኢየሱስን ለማግኘት እንዲጠበቁ በኃይማኖት አባት" ከተነገራቸው በኋላ ይህው ድርጊት አጋጥሟል።

ፖሊስ ባደረገው የነፍስ አድን ጥረት 11 ሰዎችን በህይወት ማትረፍ ችሏል። በህይወት ከተረፉት መካከል ስድስቱ የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን በከፋ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ተጠቁሟል ። ሌሎች የቀሩ ሰዎች በጫካ ውስጥ እንዳሉ መነገሩን ተከትሎ ፖሊስ ዛሬ ጠዋት ተጨማሪ ኃይል በማሰማራት ፍለጋ እንደሚቀጥል ገልጿል።

ፖሊስ በጫካው ውስጥ በቅርብ ቀናት የተቀብሩ ሰዎች አስክሬን ማግኘቱን አስታውቋል። ግለሰቦቹ ፈጥነው ወደ መንግሥተ ሰማያት ለመድረስ በረሃብ እንዲሞቱ ያደረገው የጉድ ኒውስ ኢንተርናሽናል ቤተክርስቲያን መሪ መሆኑ ተነግሯል።

#ዳጉ_ጆርናል
15.8K views14:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 19:40:54
በአልን ምክንያት በማድርግ

➨ ከ 25 - 35% ቅናሽ በእያንዳንዱ አፓርታማዎች ላይ

  የካሬ አማራጮች፦

          107 ካሬ
          110 ካሬ
          115 ካሬ
          120 ካሬ
          127 ካሬ
          138 ካሬ
          145 ካሬ
          161 ካሬ

በተጨማሪ 145 ካሬ G+1

ቤት በአገር ቤት ከአያት

መልካም ትንሳኤ

@Tsion_won

https://t.me/nvhfjnfdhnojbfedgjn

ለበለጠ መረጃ (Whatsapp/direct)፦ በ 0904444670 ወይም 0912287354 ይደውሉ
703 views16:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 19:40:06
ለልጃቸው የልብ ሕክምና ያሰባሰቡትን ገንዘብ ለልብ ማዕከል ድጋፍ አደረጉ!
ዶ/ር ሁንዴ አህመድ በጅማ ሆስፒታል ውስጥ የሚያገለግሉ የሕፃናት ኃኪም ሲሆኑ ከልብ ሕመም ጋር የተወለደ ልጃቸውን ለማሳከም የተለያዩ ጥረቶች አድርገው ሳይሳካ የልጃቸው ሕይወት ቢያልፍም እንደ አማራጭ ወደ ውጪ ሃገር ወስዶ ለማሳከም ያሰባሰቡትን የ300 ሺህ ብር የገንዘብ ድጋፍ ሌሎች ሕፃናት ይዳኑበት ብለው ለልብ ማዕከል ለግሰዋል፡፡
722 views16:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 12:11:38
63 ኢትዮጵያውያንን ያሰረው የታንዛኒያ ፖሊስ አርባዎቹን እያደነ ነው ተባለ

ሐሙስ ሚያዚያ 5 ቀን 2015 (አዲስ ማለዳ) የታንዛኒያ ፖሊስ ሕገወጥ ስደተኞች ናቸው ያላቸውን 63 ኢትዮጵያውያን ያሰረ ሲሆን፤ በሽሽት ላይ ያሉ ቀሪ 40 ስደተኞችን እያደነ መሆኑ ተገልጿል፡፡

ወደ ታንዛኒያ በሕገወጥ መንገድ በመግባት ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመሄድ ያቀዱ 100 የሚደርሱ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በመኪና ተጭነው ሲጓዙ በፖሊስ መያዛቸው ነው የተነገረው፡፡

ስደተኞችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረው የጭነት መኪና ንጆምቤ በተባለ አውራጃ አደጋ ከደረሰበት በኋላ ለመቆም ቢገደድም 40 ያህል ስደተኞች ማምለጣቸው ተጠቅሷል፡፡

ድካም ውስጥ የነበሩ 63 ስደተኞችን ከእርሻ ቦታዎች ለቃቅሞ ወደ እስር ቤት የወረወረው የታዛንያ ፖሊስ፤ 40ዎችን ለመያዝ እያፈላለገ መሆኑን ዘኢስት አፍሪካ ዘግቧል፡፡

ከምስራቅ አፍሪካ ተነስተው ወደ ደቡብ አፍሪካ ለሚገቡ ሕገወጥ ስደተኞች ታንዛኒያ ቀዳሚ መተላለፊያ መሆኗ ይነገራል፡፡

የኢትዮጵያ ስደተኞችም ከኬንያ ናይሮቢ እና መምባሳ ከተሞች ተነስተው ወደ በሕገወጥ መንገድ ታንዛኒያ የገቡ መሆናቸውን ፖሊስ አረጋግጫለሁ ብሏል፡፡

ደቡብ አፍሪካ፣ ሞዛምቢክ፣ ናሚቢያ እና ቦትስዋና ከምስራቅ አፍሪካ ለሚነሱ ሕገወጥ ስደተኞች የመጨረሻ መዳረሻዎች እንደሆኑም ተጠቁሟል፡፡

በዚህ ወቅት በታንዛኒያ እስር ቤቶች ከ4 ሺሕ 400 በላይ ሕገወጥ ስደተኞች አሉ የተባለ ሲሆን፤ የአገሪቱ መንግሥት በየዓመቱ ከ2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር በላይ ለሆነ ወጭ ይዳረጋል ተብሏል፡፡

አዲስ ማለዳ
11.4K views09:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 10:53:42
የአዲስ ዘይቤው መስራች ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ አስፋው መታፈኑ ተነገረ

አዲስ ዘይቤ በተሰኜ የዩቱዩብ ቻናሉ በሳል ፓለቲካዊ ትንታኔው የሚታወቀው ዜጠኛ ቴዎድሮስ አስፋው የፀጥታ ሀይል ነን ያሉ አፋኝ ሀይሎች ከቤቱ እንደወሰዱት ወላጅ እናቱ ተናግረዋል።
12.7K views07:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 10:52:14
የኢትዮ 251 ሚዲያ ስቱዲዮ በፀጥታ ኃይሎች ከበባ ላይ መሆኑ ተገለፀ።

ሚያዝያ 05 ቀን 2015 ዓ.ም


አራት ኪሎ "ድንቅ ሥራ ኮምፕሌክስ" ህንጻ ላይ የሚገኘው የኢትዮ 251 ሚዲያ በፀጥታ ኃይሎች ከበባ እንደተፈፀመበት የአይን እማኞች ከቦታው ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጸዋል።

ከበባውን የፈፀሙት የኢትዮጵያ ፌድራል ፖሊስ አባላት እንደሆኑ እና አሁንም ድረስ 8ተኛ ፎቅ ላይ እንደሚገኙ የመረጃ ምንጮቻችን ተናግረዋል።

መጋቢት 10 ቀን 2015 ዓ.ም ኢትዮ 251 ሚዲያ በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ሚዲያው ዘረፋ እንደተፈፀመበት ይታወቃል።

ከበባ የተፈፀመበት የኢትዮ 251 ሚዲያ ስቱዲዮ አራት ኪሎ ሚዲያ እና ነገር ወልቃይት ሚዲያ በጋራ የሚጠቀሙበት መሆኑ ይታወቃል።

የነገረ ወልቃይት ሚዲያ የበላይ ኃላፊ ዶ/ር አሰፋ አዳነ በአዲስ አበባ መታሰራቸው ይታወቃል። የአራት ኪሎ ሚዲያ መሥራችና ባለቤት እንዲሁም አዘጋጅ የሆነው ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው በትላንትናው ዕለት በመከላከያ ሰራዊት አባላት እና የደህንነት ሰዎች ታፍኖ የት እንደደረሰ ማወቅ አልተቻለም ሲል አሚማ ዘግቧል።

አሻራ ሚዲያ
12.5K views07:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 14:55:22
ለግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በአዲስ መልክ ፍቃድ ለመስጠት የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን ገለጸ።


የፌዴራል የትምህርትና ሥልጠና ባለሥልጣን የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በአዲስ መልክ ፈቃድ ለመሥጠት የሚያስችለውን ምዝገባ እያካሄደ ይገኛል።

የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ሽፈራው ሽጉጤ ለኢዜአ እንደገለጹት ተቋማቱን በአዲስ መልክ መመዝገብና ዕድሳት መስጠት በዘርፉ የሚታየውን ሕገ-ወጥ አሰራር ለመከላከል ያስችላል ብለዋል።

ተቋማቱ ከሚነሱባቸው ሕገ-ወጥ ተግባራት መካከል ፍቃድ ባልተሰጠባቸው የትምህርት መስኮችና ካምፓሶች ማስተማርን ጨምሮ ከተፈቀደላቸው በላይ ተማሪዎችን ተቀብሎ የማስተማርና ሐሰተኛ ማስረጃ የመስጠት ተግባር ይገኝበታል።

በአሁኑ ወቅት በዘርፉ ያሉት መመሪያዎችን የማሻሻል ሥራ መጠናቀቁን ያመለከቱት ዋና ዳይሬክተሩ ወደ ሥራ ከመገባቱ በፊት ከግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር ውይይት እንደሚደረግ ገልጸዋል።

ውይይቱ በትምህርት ጥራት ላይ ክፍተት እንዲፈጠር ምክንያት የሆኑ አሰራሮችን በተደራጀ መንገድ ለመቀነስና በሂደትም ለማስወገድ የሚያስችል መሆኑን ጠቁመዋል።

በዘርፉ የተሻሻለው መመሪያ በግል የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ እንደሚያግዝ ተናግረዋል።

ባለሥልጣኑ ከሕዳር 30 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ አዲስ ለሚከፈቱ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፈቃድ መሥጠት ማቆሙንም ተናግረዋል።

ምዝገባውን በዘንድሮ ዓመት በማጠናቀቀም በመጪው የ2016 ዓ.ም አዲስ ፍቃድና የእድሳት አገልግሎት መስጠት ሊጀመር እንደሚችል ነው የገለጹት።

በመሥራት ላይ ያሉ ሁሉም የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሙሉ በተቀመጠው የመመዘኛ መስፈርት መሰረት እንደ አዲስ ምዝገባ መፈጸም እንደሚጠበቅባቸውም አሳስበዋል።

(ኢፕድ)
13.1K views11:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 19:58:37
በቆቦው ግጭት ኹለት የካቶሊክ ርዳታ ሠራተኞች ተገደሉ
source VOA
በኢትዮጵያ የአማራ ክልል ውስጥ፣ የመንግሥትን የልዩ ኃይል መዋቅራዊ ለውጥ ውሳኔ በመቃወም በተቀሰቀሰው ሁከት፣ ኹለት የካቶሊክ ርዳታ ሰጪ ሠራተኞች መገደላቸውን፣ የርዳታ ቡድኑ አስታወቀ።

ሠራተኞቹ የተገደሉት፣ ባለፈው እሑድ እንደነበረ የጠቀሰው አሶሽየትድ ፕሬስ፣ መንግሥት በአገሪቱ የሚገኙ የ11 ክልሎች ልዩ ኃይሎችን መዋቅር አፍርሶ ወደ ፌዴራል ኃይሎች ለመቀላቀል ያሳለፈው ውሳኔ፣ ሕዝባዊ ዐመፅ መቀስቀሱን በዘግባው አመልክቷል።

በኢትዮጵያ ላለፉት 60 ዓመታት ሲንቀሳቀስ መቆየቱን የገለጸው የርዳታ ቡድኑ በአወጣው መግለጫ፣ ቹል ቶንጊክ የተባለው የጸጥታ መኰንኑና አማረ ክንደያ የተባለ አሽከርካሪ፣ እሑድ ዕለት ወደ ዐዲስ አበባ በመመለስ ላይ እያሉ “በጥይት ተመተው ተገድለዋል” ያለ ሲኾን፣ ስለ ግድያው ዝርዝር መረጃ አለመኖሩን ገልጿል።

በጉዳዩ አሳሳቢነት ምክንያት ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁ ሦስት የሰብአዊ ርዳታ ሓላፊዎች ለአሶሽየትድ ፕሬስ እንደተናገሩት፣ ግድያው የተፈጸመው፥ ባለፈው እሑድ፣ በቆቦ ከተማ አቅራቢያ፣ በፌዴራሉ የመከላከያ ሠራዊት እና በአማራ ክልል ኃይሎች መካከል በተፈጠረ ግጭት ነው።
11.8K views16:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ