#ሰበር
አቶ ስንታየሁ ቸኮል የዋስ መብት ተፈቀደላቸው።
በ እስር ከሁለት ወራት በላይ የቆዩት የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ኃለፊ እና የስራ አስፈፃሚ አባሉ አቶ ስንታየሁ ቸኮል ዛሬ በልደታ ፍ/ቤት በቀጠሯቸው ቀርበው ነበር። ፍርድ ቤቱም በ10,000 ብር ዋስ እንዲወጡ ፈቅዷል።
በአሁኑ ሰአት የዋስ ብሩ ተከፍሎ የመልቀቂያ ወረቀቱ ታስረው ወደሚገኙበት የፌደራል ፖሊስ ተወስዷል። ቤተሰቦቹ ከእስር ቤቱ እስኪለቀቁ እየጠበቁ ይገኛሉ።