Get Mystery Box with random crypto!

ፍቅረኛውን በጩቤ ወግቶ ለማምለጥ የሞከረው ግለሰብ ጅብ ገጥሞት ባሰማው የድረሱልኝ ጥሪ በቁጥጥር ስ | Muktarovich Ousmanova

ፍቅረኛውን በጩቤ ወግቶ ለማምለጥ የሞከረው ግለሰብ ጅብ ገጥሞት ባሰማው የድረሱልኝ ጥሪ በቁጥጥር ስር ዋለ

በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ቀበሌ ዐ1 ልዩ ቦታው ፖራዳይዝ ሆቴል ፍቅረኛውን በጩቤ ወግቶ ጫካ በመግባት ለማምለጥ የሞከረው ግለሰብ ጅብ ገጥሞት ባሰማው ጩኸት በቁጥጥር ስር መዋሉን የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል።

ግለሰቡ ከጅማ ዞን ሊሙ ሰቃ ወረዳ የአቃቢ ህግ ባለሙያ መሆኑንና ቴዲ ድሪባ እንደሚባል የመምሪያው የኮሚኒኬሽንና ሚዲያ ዋና ክፍል ኃላፊ ምክትል ኮማንደር ዮሀንስ በየነ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡

ግለሰቡ የ4ኛ አመት የዩንቨርሲቲ ተማሪ የሆነችውን ፍቅረኛውን ለመጠየቅ ወደ ደብረማርቆስ መምጣቱ ተነግሯል።በሰዓቱ ተጎጂ የሆነችው ግለሰብ ከዚህ በኋላ አንድ ላይ መቀጠል እንደማይችሉ ስትነግረው በጩቤ ወግቶ በጫካ አድርጎ ሲያመልጥ ከምሽቱ 5:00 አካባቢ ጅብ አግኝቶት አላሳልፈው ሲል ባሰማው የድረሱልኝ ጩኸት የመንቆረር ኮንስትራክሽን ጥበቃዎች ደርሰው ለፖሊስ በሰጡት መረጃ በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተጣራ እንደሆነ ተገልፆል፡፡

ግለሰቧ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባት ህክምና እየተደረገላት መሆኑን የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የኮሚኒኬሽን እና ሚዲያ ዋና ክፍል ኃላፊ ምክትል ኮማንደር ዮሀንስ በየነ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡

Via: ዳጉ ጆርናል