የአዲስ ቴሌቪዥን ዜና አንባቢ ሳህለገብርኤል ይትባረክ በጠዋት የዜና ማንበብ ክፍለጊዜ ሰአቱን ጠብቆ ጥቁር በመልበስ ዜና ማንበብ ቢጀምርም ከስቱዲዮ አቋርጠው እንዲወጣ አድርገውታል ተብሏል:: በዚህ የዜና ሰአት ፋንታም ሌሎች ፕሮግራሞች ተለቀውበታል::
በተመሳሳይ የጣቢያው ጋዜጠኞች እና የአገልግሎት ዘርፍ ሰራተኞችም ጥቁር በመልበሳቸው ምክንያት ከግቢ እንዳይገቡ ታግደዋል::
በትናንትናው እለትም ተመሳሳይ ችግር ተፈጥሮ ሰራተኞች ተመልሰው እንደነበር በተለያዩ የሚዲያ አውታሮች መዘገቡ አይዘነጋም::
ሮሐ ኒውስ