Get Mystery Box with random crypto!

የስብዕና ልህቀት

የቴሌግራም ቻናል አርማ human_intelligence — የስብዕና ልህቀት
የቴሌግራም ቻናል አርማ human_intelligence — የስብዕና ልህቀት
የሰርጥ አድራሻ: @human_intelligence
ምድቦች: መዝናኛዎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 90.41K
የሰርጥ መግለጫ

በዚህ ቻናል
⚡ህይወትን የሚያንፁ የስነ-ልቦና ምክሮች
⚡መሳጭ የፍቅር ታሪኮች እና ወጎች
⚡ጥልቅ ማህበራዊ እና ፍልስፍናዊ እይታዎች
⚡ውብ የጥበብ ስራዎች
በፅሁፍ እና በድምፅ/Audio ይቀርባሉ።
#ሼር በማድረግ ወዶጅዎን የዚህ የእውቀት እና የጥበብ ድግስ ታዳሚ እንዲሆኑ ይጋብዙ።

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2024-02-25 21:40:13 “ጅል አይሙት እንዲያጫውት!”
ከአሌክስ አብርሀም
መፅሀፍ-አልተዘዋወረችም

በአገራችን ባህል የዝምታ ትርጉም ግራ የገባው ነው፡፡ እውነት በአደባባይ ሲደፈጠጥ እያዩ አፍን መሸበብ፤ ግን ደግሞ በስሚ ስሚ ለመጣ አሉባልታ ነፍስን ጭምር መስጠት። ጮኾ የማያወራ፣ ሐሳቡን የማይገልጽ ሕዝብ የሐሜት ጫካ ነው። በየጋራና ሸንተረሩ ጥይት ከማስጮኸ የበለጠ፣ ጮኽ ብሎ ያመኑበትን መናገር የሚከብደው ሕዝብ ጀግንነቱ ከባድ ጥያቄ ውስጥ ነው፡፡ በዝም አይነቅዝም ብሒል የነቀዘ ሕይወት እንመራ ዘንድ የፈቀድን ሕዝቦች መሆናችን ሳያንስ ይኽንንም ባህል አድርገን ልንኮራበት ይዳዳናል፡፡

ይኼ ተወልጄ ያደግሁበት ሕዝብ በሹክሹክታ ያወራል፣ ጓዳ ለጓዳ ያወራል፣ እውነት ይሁን ውሸት አግበስብሶ ያወራል፣ እንደ ወረርሽኝ ወሬ በብርሃን ፍጥነት ያዛምታል፣ በአደባባይ ግን ዝምተኛን ያደንቃል- ያበረታታል፡፡ በተረቱ “ዝም ባለ አፍ ዝንብ አይገባም” እያለ  ዝንብ ፈርቶ ዝም (እንዴት _ ለዝንብ ዝም ይባላል? ለምን ሰፈራችሁን አጽድታችሁ እንደልባችሁ አታወሩም? የሚል የማሪያም ጠላት ነው!) መንግሥትን ፈርቶ ዝም (እንዴት ዝም በሉ ለሚል መንግሥት ዝም ይባላል አፋኝ መንግሥት እጁን ከአፋችን ላይ እንዲያነሳ መንገር የለብንም ወይ? የሚል የአገር ጠላት ነው) ይሉኝታን ፈርቶ ዝም (እንዴት በይሉኝታ እንለቅ? ብንል የባህል ጠላት መባል ይመጣል፡፡)


ሁሉም ስሕተትና ፍርኃታችን እንደ ትልቅ ሐብት በእሳት ሰይፍ ተከቦ የሚጠበቅ ቅርስ ነው፤ እውነት ብቻ ነው ራቁት፡፡ ለዚያም ሳይሆን አይቀርም እውነት የእብዶችና ሰካራሞች ልፈፋ ተደርጋ በየመድረኩ የምትሳለው፡፡ እብዶች እውነቱን እንዲናገሩለት “ጤነኛው' ከፍሎ ይታደማል፡፡ ይኼ ባህላችን ሲሆን ከያኒ የነፍሱን ጥሪ ጥሎ የጅሎች አፈቀላጤ ይሆናል፡፡ ታዲያ የዚህ ሁሉ ምክንያት ፍርኃታችን ቢሆንም፣ ይኼንንም በሰበብ ስንጀቡነው (መቼም ሰበብ አናጣ) “ዝምታችን ትዕግስት የወለደው፤ ትዕግስታችንም አምላካችንን የምንፈራ ሕዝቦች ስለሆንን የተጎናጸፍነው ጸጋ ነው” እንላለን፡፡ እውነታው ግን አምላክን መፍራታችን ሳይሆን ፍርኃትን ማምለካችን ነው።

በዚህ ሁሉ ዝምታ ውስጥ የታቀፈ ጅልነት ድርጊት ሆኖ ሲፈለፈል ከግለሰብ እስከ አገር ስንት የጨነገፈ ኑሮ ፈጠረ!? ታዲያ የራሳችን ዝምታ ተጠራቅሞ ሲከብደንና አላራምድ ሲለን፤ በየዘመኑ ጊዜና ሁኔታ እየጠበቅን በጋራ እንጮኻለን። የጨረባ ተዝካር! ይኼን ዓይነቱን ጩኸት አብዮት እንለዋለን (የታዘዙትን ሁሉ እሺ! እያሉ አብዮት አለ ወይ?!) ነገሩ ልክ ውሃ ውስጥ የተነከረ ውሻ፣ ውሃውን ከላዩ ላይ ለማራገፍ በደመነፍስ እንደሚርገፈገፈው ዓይነት ነው፤ ውሃው ቢራገፍም ውሻው ያው ውሻ ነው፡፡ አጯጯኻችን በአንድ ላይ በየአፋችን ስለሆነ ማንም ማንንም አይሰማም፤ ማንም የማይሰማው ጩኸት ደግሞ ከዝምታ እኩል ነው፡፡

ይኼ ዝምታ፣ የጅል ባንዲራ እንጂ ጨዋነት አይደለም። ባንዲራችን ከፍ ብሎ የሚውለበለበው ለዘመናት በተከመረና በደደረ ጅልነታችን ላይ ይመስለኛል፡፡ የባንዲራችንን ቀለም እየጠቀስን የማንሰጠው ትርጉም የለም። ሁሉንም ቀለም እንደ ዳማከሴ ጨቅጭቀን ብንጨምቀው ከጀግንነታችንም በፊት፣ ከኩሩነታችንም በፊት፣ከአገር ፍቅራችንም በፊት የሚንጠባጠበው ጅልነታችን ሳይሆን ይቀራል?!

እሱን እየተቀባን ስንት ጊዜ ከዘመን በሽታ ተፈወስን ብለናል?! ፈውሳችን ሐሰት ነበርና ምስክርነታችን የታተመበት ቀለም ሳይደርቅ፣ ብዙዎች በነጠላም በጅምላም የጅል በትር ሰለባ ሆነው ወደ መቃብር ወርደዋል፡፡


የተረፍነው እንዴት ተረፍን? እያልኩ ሳስብ፣ አንዳንዶች “ምሕረቱ በዝቶልን'' ቢሉም እኔ ግን ፈጣሪም ከዚህች ከኛ ምድር በተዋሰው ተረት “ጅል አይሙት እንዲያጫውት!” ብሎ ለአጫዋችነት ትቶን ይሆናል እላለሁ፡፡ አገሬ ጨዋታና ተጨዋች ይበዛታል፡፡ እንደ አገር ልጅነታችንን አልጨረስንም ይሆን? እስከምል ድረስ የአገሬ ጨዋታ ወዳድነት ያስደምመኛል፡፡

ጅልነቴ ከሕዝብ ባሕር የተቀዳ ነው ስል፣ ለጥፋቴ ሌላ የሕዝብ ክንብንብ ውስጥ መደበቄ አይደለም፤ ምንስ ቢሆን ሕዝብ የሚባለው አጀብ ለሚሊዮኖች ቢሰነጣጠር አንዱ ስንጣሪ መሆኔ አይቀር፡፡ ሕዝባዊ ጀግንነት፤ ሕዝባዊ ታሪክ እንዳለ ሁሉ ከየቤታችን አዋጥተን አገራዊ ያደረግነው ሕዝባዊ ጅልነት አለመኖሩን ማን አጥንቶ ነገረን?! ጅልነት ቀለም ነው፤ ታሪካችን እኛም በግልና በጅምላ አማርን ብለን የተቀባነው የተኳኳልነዉ ጠይም ቀለም፡፡ በዚህ ጠይምነት በኩል ስለተገለጠ ግለሰባዊ ጅልነቴ በጸጸት አወራለሁ... በጓዳዬ ለአገር ያዋጣሁት የጅልነት ድርሻ... ይኽም ከንስሓ ይቆጠር እንደሆን እንጃ፡፡

@zephilosophy
@zephilosophy
12.6K views18:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-17 21:39:59 ጣፋጩ ገዳይ መርዝ!

በሰሜን አንታርቲካ ላይ የሚኖሩ እስኪሞ የተባሉ ጎሳዎች ተኩላ ለመግደል ሲፈልጉ የሚዘይዱት ዘዴ አለ፡፡ በበረዶ ውስጥ ጫፉ በጥቂቱ የወጣ ቢላ ይደብቃሉ፤ በላዩ ላይ ጥቂት የበግ ደምን ያደርጉበታል:: ተኩላው ደሙን አሽትቶ ይመጣል፡፡ በረዶው ላይ ያለውን ደም መላስ ይጀምራል።

ደሙ ይጣፍጠዋልና ፍጥነቱን እየጨመረ መላስ ይጀምራል፡፡ በዚህ ፍጥነት ውስጥም እያለ ሳያስበው ደም የተቀባው ቢላዋ ምላሱን ይቆርጠዋል፡፡ ነገር ግን ደም መላሱን አያቆምም፡፡ አሁን ላይ ይህ ተኩላ ባለማወቅ ከራሱ ምላስ የሚፈሰውን ደም እየላሰ ነው፣ ሆኖም ጣፍጦታል እና በፍጥነት መላሱን ይቀጥላል። ከመጠን በላይ ደምም ይፈሰዋልና በነጋታው ተኩላው ሞቶ ይገኛል። የራሱን ደም እየጠጣ እንደነበረም አልታወቀውም።

ይህ ተኩላ ከእኛ ታሪክ ጋር ይቆራኛል፡፡ ብዙዎቻችን ጊዜያችንን የምናሳልፈው በስልካችን ላይ አልያም በቴሌቪዥን ላይ ነው... ጊዜያችንን ሳንጠቀምበት እንዲሁ ያልቃል... ይጣፍጣልና፤ ጥቂት ብቻ አይበቃንም፤ በፍጥነት እና በኃይልም ህይወታችንን፣ ጊዜያችንን ልሰን እየጨረስነው ነው:: በተቻለህ መጠንም ከስራህ እና ከማሰብ ከሚያስተጓጉሉህ ነገሮች ሁሉ ለማራቅ ሞክር።

ድብቁ አእምሮ ድብቁ ኃይል

@Human_Intelligence
13.1K views18:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-09 07:35:04 የተወሰደውን ሕይወታችሁን አስመልሱ!

ሕይወታችንን ማስመለስ ማለት በአጭሩ ሲተረጎም በአንድ ሰው፣ ሁኔታ ወይም ልምምድ ምክንያት ከደረሰብን ቀውስ የተነሳ በትክክል ማሰብ፣ መስራት፣ መተኛትም ሆነ መኖር እስከማንችል ድረስ የደረሰውን ሁኔታችንን እንደገና ወደቀድሞው ጤናማ ሁኔታ ማስመለስ ማለት ነው፡፡

•  የጎዳችሁና እስክትበቀሉት ድረስ ውስጣችሁን የሚያናድደው ሰው የወሰደባችሁን ሕይወታችሁን አስመልሱ!

•  ሰዎችን አምናችሁ በተወሰደባችሁ ቁሳቁስ ወይም ገንዘብ ምክንያት ዘወትር ከመቆጨታችና ከመቆዘማችሁ የተነሳ የተወሰደውን ሕይወታችሁን አስመልሱ!

•  አፍቅራችሁ ትንሽ ከተጓዛችሁ በኋላ ያ ሰው ለእናንተ ምንም ፍላጎት እንደሌለው ብትደርሱበትም ካላችሁ የስሜት ትስስር የተነሳ ልትረሱት ባልቻላችሁት ሰው የተወሰደውን ሕይወታችሁን አስመልሱ!  

•  ማንኛውንም ሰውም ሆነ ሁኔታ ከመፍራታችሁ የተነሳ ወደፊት መራመድ እስከማትችሉ ድረስ በመሆናችሁ ምክንያት የተወሰደውን ሕይወታችሁን አስመልሱ!

ወደራሳችሁ ተመለሱ! ወደቀደመው ሰላማችሁ ተመለሱ! ወደእውነተኛው ማንነታችሁ ተመለሱ! ከምንም ሁኔታና ከማንም ሰው ጫና ውጪ ወደነበራችሁበት ሚዛናዊ ሕይወት ተመለሱ!

ንቁ! ወስኑ! ምክርና እገዛን ፈልጉ! የድሮውን ጤናማ ማንነታችሁን እንደገና የራሳች አድርጉ እንጂ የሰውና የሁኔታዎች ሰለባና መጫወቻ አትሁኑ!

መልካም ቀን!

Dr eyob
12.9K views04:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-01-18 22:35:48 #የተፈጥሮ_ዑደት

በተፈጥሮ ዑደት ውስጥ ድል ማድረግም ሆነ ድል መሆን የሚባሉ ነገሮች የሉም። ያለው እንቅስቃሴ ብቻ ነው:: ክረምት ከሁሉም የበላይ ሆኖ እስከመጨረሻው ለመዝለቅ ይጣጣራል:: ሆኖም ጊዜውን ጠብቆ የፀደይን ተተኪነት ከመቀበል በቀር አማራጭ አይኖረውም፡፡ ፀደይም አበቦችን እና ፍካትን እንዲሁም ደስታን ይዞ ከተፍ ይላል። በጋውም ቢሆን ሞቃታማ ቀናቱን ለዘለዓለም ለማዝለቅ መውደዱ አይቀርም:: ነገር ግን የበልግን መምጣት ተቀብሎ ስፍራውን አስረክቦ ዘወር ይላል:: በልግም ምድሪቱ ታርፍ ዘንድ እድል ይሰጣታል::

አጋዘን ሳርን ብትበላም እርሷ ራሷ የአንበሳ ምግብ ናት:: ይህ የጥንካሬ ጉዳይ አይደለም:: ማን ይበልጥ ይበረታል ስለማለትም አይደለም:: ይልቁን አምላክ የሞትንና የትንሳኤን ዑደት ለእኛ የሚያሳይበት መንገድ ነው:: በዚህ ዑደት ውስጥም አሸናፊም ተሸናፊም የለም:: መታለፍ ያለባቸው ደረጃዎች ብቻ እንጂ። የሰው ልጅ ልብ ይህንን እውነታ ሲረዳ ነፃ ይሆናል፤ አስቸጋሪ ወቅቶችን ለማለፍ አያዳግተውም፤ በድል አድራጊነት የሞቅታ ስሜትም አይታለልም:: ሁለቱም አላፊ መሆናቸውን አይዘነጋም:: አንዳቸው በሌላቸው ይተካሉ::

ዑደቱም ይቀጥላል::

ስለዚህ የፍልሚያ ቀለበት ውስጥ ያለ ቡጢኛ (የራሱ ምርጫ አሊያም ሊመረመር የማይችል እጣ ፈንታ እዚያ ያስገኘው) ከፊት ለፊቱ በሚጠብቀው ፍልሚያ ተስፋ በደስታ ስሜት ውስጥ ሊዘፈቅ ይችላል፡፡ ክብሩንና ግርማውን መጠበቅ ከቻለ ፍልሚያውን ቢሸነፍም እንኳ ተሸናፊ ሊባል አይችልም:: ምክንያቱም መንፈሱ ምንም አልተሸራረፈምና።

ስለደረሰበት ነገር ሁሉ ሌሎችን መውቀስን ሙጥኝ አይልም፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ አፍቅሮ፤ የፍቅር ጥያቄው ውድቅ ከተደረገበት
ጊዜ አንስቶ ይህ ውድቀት በእርሱ የማፍቀር ችሎታ ላይ ያመጣው አሉታዊ ለውጥ እንደሌለ ያውቃል::

በፍቅር ውስጥ እውነት የሆነው ሁሉ በጦርነት ውስጥም ይሰራል።

ፓውሎ ኮሆልዮ
@Human_Intelligence
16.8K views19:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-01-14 21:45:39 አክሱም ላይ አንቀላፍቶ
ማይጨው ላይ መንቃት
የቀጠለ

ነገርግን አክሱምን፣ ላሊበላን፣ ፋሲልና ጀጎልን የጠረቡ እጆች ስለምን ለሺህ ዘመናት በደሳሳ ጎጆዎች ውስጥ እንደተቸነከሩ ማሰብ ሕመምን ይፈጥራል፡፡ ፊደል ነበረን፤ እንደ ሕዝብ ከመጻፍ ይልቅ መስማትን እንመርጣለን፡፡ ይበልጡኑ መሀይማን ነበርን፡፡ በኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ አማካኝነት ሙዚቃን በኖታ በመጻፍ የመጀመሪያዎቹ ብንሆንም እዚሁ አበርክቶ ላይ ጥቂት ሀሳብ ለመጨመር የተክሌ አቋቋም, እስኪቀመር አንድ ሺህ ሦስት መቶ ዓመታት መጠበቅ ነበረብን፡፡

በ1237 ዓ.ም አካባቢ ከሦስት መቶ ዘመናት የዛግዌያን አገዛዝ በኋላ ሥልጣን በቤተክርስቲያን ጠንካራ ተጽዕኖ ከዛግዌ ነገሥታት ወደ የዘር ሀረጋቸውን ከሰሎሞን ዘር እንመዛለን ለሚሉ ሰሎሞናዊ ነገሥታት ተዛወረ፡፡ የዛግዌ ነገሥታትን ሥልጣኑን ለሰሎሞናዊው ገዥ ይኩኖአምላክ እንዲያስተላልፉ በመወትወት፣ በመገሰጽ አቡነ ተክለኃይማኖት ከፍተኛ ሚና እንደነበራቸው ይነገራል፡፡
በሂደቱም ቤተክርስቲያን እስከ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዘመነ መንግስት ድረስ የዘለቀ የክፍለዘመናት የሢሶ መንግሥትነት ፈላጭ ቆራጭነቷን አጸናች፡፡

ጥቂት ቆይቶ በ330 ዓ.ም አካባቢ የሰሎሞናዊ ስርወመንግሥቱን በትርክት እና በሕግ ለማጽናት ሲባል ‹ክብረነገሥት› የተሰኘው መጽሐፍ የመጻፉ አስፈላጊነት ታመነበት፡፡

መጽሐፉ የኢትዮጵያ ንጉሣዊ ሥልጣን ባለቤቶች የዘር ሀረጋቸውን ከንጉሥ ሶሎሞን እና ከቀዳማዊ ምኒሊክ ዘር የሚመዙ ብቻ መሆናቸውን በማያሻማ ኹኔታ ይደነግጋል፡፡ በዚህም መጽሐፍ የተነሳ ኢትዮጵያን ሀገራቸውን እንደዳግማዊት ኢየሩሳሌም እንዲመለከቷት ተበረታተዋል፡፡ ለዘመናት በክርስትና እምነት መነሻነት በተገነባው በዚህ ትርክት እና በክርስትው ኃይማኖት ምክንያት ከኢትዮጵያ ውጭ በኢትዮጵያዊያን (በሰሜነኛው ክርስቲያን) አዕምሮ የታተመች ሌላ ከተማ (ሀገር) ብትኖር ኢየሩሳሌም ብቻ ናት፡፡ በዚህ ሰበብ ይመስላል ኢትዮጵያዊያን ለዘመናት ከውጭው ዓለም የመጣውን ሰው በተለይ ክርስቲያኑን ሁሉ የኢየሩሳሌም ሰው እንደሆነ ይቆጥሩ እንደነበር በልዩ ልዩ ተጓዦች ማስታዎች ላይ ተዘግቧል፡፡

በዚህ መልኩ በአስራ አራተኛው መቶ ክፍለዘመን መጀመሪያ የተጻፈው ክብረነገሥት ከፊውዳል ሥርዓቱና ከቤተክህነቱ ጋር ተቀይጦ በኢትዮጵያ የሥነ መንግሥት ታሪክ ሰባት መቶ ዘመናት ድረስ የዘለቀ ገዥ ትርክትን ፈጠረ፡፡ ይህ ትርክት በተለይ ከሞላ ጎደል በአንድ አገዛዝ ሥር የሚያድር፣ ልዩ ልዩ ቋንቋዎችን የሚናገር በአብዛኛው የክርስትና እምነት ተከታይ የሆነውን ሰሜነኛ ሕዝብ ለሰባት ክፍለዘመናት ያስተዳደረ መሪ ትርክት ሆኖ አሳለፈ፡፡ ዳግማዊ ምንይልክ የተበታተነውን የዳር ሀገር ሕዝብ ሁሉ በአንድ አጠቃለው በዘውዳዊ ሥርዓቱ ሥር ካስገቡትም በኋላ በዚህ ትርክት ሥር እንዲመላለስ ሙከራ አድርገዋል፡፡ ሙሉ ለሙሉ የሰመረ ነበር ባያስብልም ቢያንስ በእሳቸው ዘመን ትርክቱ የአንድነት ስሜት በመፍጠሩ የአድዋ ጦርነትን የመሰለ በተባበረ ከንድ የተገኘ እጅግ አንጻባራቂ ገድል ለመከወን መሣሪያ ሆኗል፡፡

ኢጣሊያኖች ኢትዮጵያን ዳግም የወረሩ ሰሞን በቅኝ ገዥ ሴራ ሕዝቡን ለመከፋፈል አማርኛ ተናጋሪውን ሕዝብ በጅምላ የፊውዳል ሥርዓቱ ተጠቃሚ እና ጨቋኝ ገዥ መደብ እንደሆነ ፈርጀው ትርክታቸውን ማጠንጠን ጀመሩ፡፡ ይህ ትርክት በተለይ ከ1983 ዓ.ም ጀምሮ ድፍን ሃያ ሰባት ዓመታት በሕገመንግሥት፣ በመንግሥት በጀት፣ በመንግሥት መገናኛ ብዙሃናት በይፋ እና በስውር እንደ አስፈላጊነቱ ይቀነቀን ነበር፡፡ በበኩሌ ሰሜነኛው ሕዝብ ለፊውዳል ሥርዓቱና ለአገዛዙ በነበረው ጂኦግራፊያዊ ቅርበት ከሌላው ኢትዮጵያዊ ሕዝብ በተለዬ ተጠቃሚ ከመሆን ይልቅ ከሁሉም በላይ በሥርዓቱ ይበደል እንደነበር አስባለሁ፡፡

ከ2010 ዓ.ም በኋላ የመጣው አስተዳደር በመደመር ግራ የገባው ቅኝት እዚያ እና እዚህ እየረገጠ ምንም የትርክት ለውጥ ሳያስፈልገው የጨቋኝ ተጨቋኝ የትርክት ንጥቂያ እና ቁማርን ማስቀጠሉን ለመረዳት ብዙ የፖለቲካ ብስለት የሚጠይቅ አይመስለኝም፡፡

እኛ ግን ለመላው ጥቁር ሕዝብ ትርክት ቀማሪነት የታጨን ሆነን ሳለን የራሳችን የቤት ሥራ እንኳን ሰርተን ያልጨረስን መሳቂያ የመሆናችን ነገር ያሳዝናል፡፡ ታላቁ ጥቁር የተሰኘ በንጉሴ አየለ ተካ የተጻፈ መጽሐፍ ያነበበ ሰው ሁሉ ንጉሠ ነገሥቱ አጼ ኃይለሥላሴ በቅኝ አገዛዝ ቀንበር ስር ለነበሩ ጥቁር ሕዝቦች ሁሉ እንደምን ይታገሉ እንደነበር መታዘብ ይችላል፡፡

ታሪካችንን አላወቅነውም፡፡ መናናቂያ አድርግነዋል፡፡ በታሪክ አጋጣሚ ያገኘነውን በሰው ዘርን ሁሉ ፊት በግርማ ሊያስጠራን የሚችል ዕድል እንደዘበት አምልጦናል፡፡ እናስ ያቆሙን መሰረቶች ምን ያህል ጽኑዓን ነበሩ? እንደ ኅብረተሰብ የአቋራጩ፣ ልክፍተኞች ሆነን ለመገኘታችን ምክንያቱ ምንድን ነው? የምንዋቀሰው፣ የምንናናቀው በድንቁርናችን ልክ አይደለምን? ለፍጥረት ሁሉ ከሚተርፍ በረከት፣ ኅሊና እና ርህራሄ ጋር ተፈጥረን ሳለን ዘመኑን ስላለመዋጀታችን በሰንደቅ ዓላማ ለሚያስለምን ችጋር ራሳችንን አላጨንምን?

ይቀጥላል
ደራሲ-ያዕቆብ ብርሀኑ
መፅሀፍ-በፍም እሳት መቃመስ
14.9K viewsedited  18:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-01-07 12:14:34
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታይ የቻናላችን ቤተሰቦች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሰላም አደረሳችሁ።
መልካም በዓል ይሁንላችሁ ዘንድ እንመኛለን።
13.3K viewsedited  09:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-01-04 06:08:41 የልማድ ምስጢር!

“ደጋግመን የምናደርገውን ነገር ነን፡፡ ስለሆነም፣ ልቀትና ምርጥነት የአንድ ጊዜ ተግባር ጉዳይ ሳይሆን የልማድ ጉዳይ ነው” - Aristotle

“እኔ የአንተ የዘወትር አጋርህ ነኝ፡፡ ታላቅ የሆንኩ ረዳትህ ነኝ ወይም ደግሞ ከባድ የምባል ሸክምህ፡፡ ወደ ስኬት ልገፋህ እችላለሁ፣ ወይም ደግሞ ወደ ውድቀት ልጎትትህ ብቃት አለኝ፡፡ ሁል ጊዜ እንዳዘዝከኝ ለመሆን ዝግጁ ነኝ፡፡ በየእለቱ ከምታደርጋቸው ነገሮች ገሚሶቹን ለእኔ አሳልፈህ ብትሰጠኝ ባፋጣኝና በትክክለኛው መንገድ አከናውናቸዋለሁ፡፡ ጠንከርና ጨከን ካልክብኝ፣ በቀላሉ ልትገራኝና ልታስተዳደረኝ ትችላለሀ፡፡ አንድ ነገር በምን መልኩ መደረግ እንዳለበት አሳየኝና ትንሽ ካለማመድከኝ በኋላ በፈለከው ጊዜ ሁሉ በፍጥነት አከናውንልሃለሁ፡፡ ታላላቅ የተሰኙ ሰዎች አገልጋይ ነኝ፤ ሆኖም የውድቀትና ያለመሳካትም ምክንያት እኔው ነኝ፡፡ ታላላቅ የሆኑን ሰዎች ታላቅ ወደ መሆን ያመጣኋቸው፤ የወደቁና ያልተሳካላቸውንም ሰዎች ለዚያ ያበቃኋቸው እኔ ነኝ፡፡ ማሽን አይደለሁም፤ ነገር ግን ልክ እንደ ማሽን የተሰጠኝን ሁሉ ሳላዛባ፣ ልክ እንደሰው ደግሞ በብልህነት እሰራለሁ፡፡ ከፈለክ ለትርፍ ተጠቀምብኝ ካለዚያም ለክስረት ተጠቀምብኝ፣ በእኔ በኩል እንደሆነ ምንም ልዩነት አያመጣም፡፡ ውሰደኝ፣ የራስህ አድርገኝ፣ አሰልጥነኝ፣ ጠንከርና ጨከን በልብኝ እኔም በተራየ አለምን አስገዛልሃለሁ፡፡ ቀለል በልልኝና ችላ በለኝ፣ አጠፋሃለሁ፡፡ ማን ነኝ? እኔ ልማድ እባላለሁ!” – Anonymous

ልማድ ማለት በአንድ ነገር አቅጣጫ ራሳችንን ከማስለመዳችን የተነሳ ያንን ነገር በቀላሉ ማድረግ ስንጀምርና እንደውም ማቆም ሲሳነን ማለት ነው፡፡ ይህ እውነታ ደግሞ ለጤናማውም ሆነ ለጤና ቢሱ ልማድ የሚሰራ እውነታ ነው፡፡ ልማድ ማለት ካለምንም የውጭ ግፊትና ጉትጎታ ማድረግ የጀመርነውና “የማንነታችን” ክፍል ወደ መሆን የመጣ ጉዳይ ነው፡፡ ከመልካም ልማድ ውጪ ማንም ሰው ምንም ነገር ማድረግ አይችልም፡፡ በሌላ አባባል ወደ ልማድ ባልመጣ መልካም ነገር ወደ ስኬት መምጣት አንችልም፡፡

ብቃትና ጥራት ማለት የተለመደን ነገር ባልተለመደ መልኩ ማድረግ ማለት ነው፡፡ ይህ እንዲሆን ደግሞ መልካምን ልማድ ማዳበር የግድ ነው፡፡ ለምሳሌ፣ በአንድ ስፖርት ኦሎምፒክ ላይ የሚወዳደሩ ሰዎች በአማካኝ ካለማቋረጥ ለስድስት ዓመታት ሙሉ በአመት ለ310 ቀናት፣ በየቀኑ ለአራት ሰዓታት ልምምድ ያደርጋሉ፡፡ ሌሎች ሰዎች ቀኑን ሙሉ የማይሰሩትን ስራ እነዚህ ስፖርተኞች ጠዋት አንድ ሰዓት ከመሆኑ በፊት ሰርተው ይጨርሳሉ፡፡ 

አሁን ምንም አይነት የላቀ ደረጃ ላይ የደረሰን ሰው ተመልከትና ጀርባውን አጥና፤ ለረጅም ጊዜ ደጋግሞ ያደረገውንና የገነባውን አንድ ነገር ታገኛለህ፡፡ በሌላ አባባል፣ አሁን የደረሰበት የላቀ ደረጃ የደረሰው በአጋጣሚ ሳይሆን አንድን መልካም ልማድ አዳብሮና በዚያ ልማድ ዙሪያ ደጋግሞ በመስራትና በመሻሻል ነው፡፡

የንጽህና ልማድ ቤትን፣ አካባቢንና አገርን በንጽህና ልቀው እንዲገኙ ያደርጋቸዋል፡፡ የስራ ልማድ በብልጽግና ልቀን እንድንገኝ ያደርገናል፡፡ የጥናት ልማድ በእውቀት እንድንልቅ መንገዱን ይጠርጋል፡፡ ከማንኛውም ውብ ነገር ጀርባ መልካም ልማድ አለ፡፡ በእኔና በአንተም ኑሮ ስሌቱ ያው ነው፡፡

አንድ ቀን ከእንቅልፋችን ስንነሳ በአንድ ነገር ልቀን አንገኝም፡፡ ከአንድ ግብ አንጻር በየእለቱ የገነባናቸው ልማዶቻችን ናቸው የነገን ልቀታችንን የሚወስኑት፡፡ ልማድ የሕወታችንን አብዛኞዎቹን (ምናልባት ሁሉንም) ነገሮች አቅጣጫ ወሳኝ የሆነ ጉዳይ ነው፡፡ ጤንነታችንን፣ ኢኮኖሚያችንን፣ ወዳጅነታችንን የኑሮአችንን ጥራትና ሌሎችም ዋና ዋና ነገሮችን ስለሚወስን፤ ልማድ ሲጨመቅ ማንነት ይሆናል፡፡  

ዶ/ር እዮብ ማሞ
@Human_Intelligence
13.4K views03:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-12-31 20:51:11 አያ ጅቦ አለህ ? አለሁ ምን እየሰራህ ነው?....
እናንተን ልበላ

እናቴ የአምስተኛ እና የስድስተኛ ክፍል ጂኦግራፊ አስተማሪ ነበረች፤ ጡረታ ከመውጣቷ በፊት፡፡ የምታስተምርበት ትምህርት ቤት ብማርም እሷ የምታስተምርበት ክፍል አልተማርኩም። ልጆች ስለምትወድ፣ እንደ ልጆቿ ስለምትቀርባቸው እንደሚወዷት በርካታ ጊዜ ምስክርነት ሰምቻለሁ፡፡ አሁን እንኳን ጡረታ ወጥታ መንገድ ላይ ያስተማረቻቸው ተማሪዎች ፍቅር እና አክብሮታቸውን ሲገልጹላት ብዙ ጊዜ አይቻለሁ።

እናቴ የላላ፣ የተቆጠበ ማኅበራዊ ግንኙነት ያላት፣ ረጋ ያለች፣ ፈገግታ የማይለያት ደርባባ ሴት ናት። ሙሉ ጸጉሯ ሃጫ በረዶ መስሎ ጥቁር ነበረው ቢባል ለማመን ይቸግራል። ብቻዋን ነው ያሳደገችኝ፡፡

ልጅ ሳለሁ እቴቴ አባቴ የት ነው ያለው? እላታለሁ፡፡

“ይመጣል ሰላም ለማስፈን ነው የሄደው” ትለኝ ነበር!! በስንት ተረት ሰላም ምን ማለት እንደሆነ ከገባኝ በኋላ ሁከት እና ግርግር ሳይ አባቴ አልደረሰም ማለት ነው እያልኩ፣ ሲደርስ አባቴ ሁሉን ያስተካክላል እያልኩ አደግሁ።
ሲደርስ ሰላም ይሆናል።

"ትንሽ ነፍስ ሳውቅ አባቴ ጦርነት እንደሄደ፣ እናት ሀገሬ ብሎ ሸልሎ ወጥቶ አድሮ ወጥቶ መቅረቱ ተገለጸልኝ። አባቴ እንዴት ነበር? እለዋለሁ ከእኔ በዕድሜ በልጦ ተወልዶ በጥቂትም ቢሆን አባቴን የሚያውቀው ወንድሜን።

“አባታችን ተጫዋች፣ እናታችንን የሚንከባከብ፣ ደ'ሞ ደ'ሞ ከሥራ ማታ ሲመጣ ሁሌም በፌስታል ለእኛ አንድ ነገር ሳይዝ የማይመጣ፤ ከሥራ ደክሞት እንኳን መጥቶ ሳያጫውተን የማያድር ነበር” እያለ ይተርክልኛል።

በትንሹም በትልቁም አባቴ ቢኖር እላለሁ፤ ጉድለቱ ሲሰማኝ... አባት እና ልጅ ሲሄዱ የልጁ ዕድለኝነት ሲታየኝ የአባት ፍቅር ጉድለት ስሜት እየጠዘጠዘኝ፣ እኔም እንደ ማደግ ወንድሜም ለአቅመ አዳም ደረሰ።
ወንድሜ ሥልጣን ላይ ያሉትን የአባቴን ገዳዮች ለመታገል ፖለቲካን ማደሪያው አደረገ። ተቃዋሚ ነን ካሉት ጋር ሁሉ ቀድሞ ይሰለፋል፡፡ ሁሌም የተቃዋሚዎች ባንዲራ ያዥ እሱ ነው፡፡ ደፋር ነው ይሉታል።

አንድ ቀን ማታ እናቴ “ወንድሜ ቤት አላደረም” ብላ ሀገር ይያዝ አለች... ፈለገች፣ አስፈለገች... እሱን የበላ ጅብ አልጮህ አለ። ከጥቂት ቀን በኋላ ግን መታሰሩን ሰማን... እናቴ አነባች፣ ተንገበገበች! ያኔ ነው ለመጀመሪያ ጊዜ ከፍቶኝ ስቅስቅ ብዬ ያለቀስኩት። ንፍጤን እና እንባዬን እየጠረግኩ አይመጣም እኮ እሱም እንደ አባዬ አይመጣም በኋላ ማንም የሚያግዝልኝ፣ ወንድሜ አይመጣም
የሚያስጠናኝ አይኖርም... እያልኩ አለቀስኩ!

በወንድሜ መታሰር ድብርት ይሆን ብቸኝነት የሆነ ውሉ የማላውቀው መንፈስ ወረረኝ። ደፋር እኮ ነው እያሉ ከፊት ሲያሰልፉት የነበሩት ሰዎች አንድ ቀን እንኳን ለመጠየቅ አልደፈሩም፡፡ የታሰረበትን የሚነግረን አጥተን ስንከራተት ያውቁ እንደሆን ስንጠይቃቸው እሱን ራሱ አናውቀውም አሉን፡፡

እናቴ የተነሳውን ርእስ ወደ ወንድሜ ስባ አምጥታ “አሄሄሄሄ ያልታደልኩ” ትላለች። በሰልኩ መሰለኝ ድሮ ስለ አባቴ እያወራችኝ ስታለቅስ፣ ሕመሟ ስለማይገባኝ ጀመራት የምል የነበርኩ ልጅ ዛሬ እኔ አለሁልሽ እያልኩ አጽናናት ጀመር።

ወንድሜ በታሰረ በሁለተኛ ወሩ እስር ቤት ውስጥ በተፈጠረ ጠብ መሞቱን ፖሊሶች ቤታችን መጥተው ሦስት መሥመር በማትሞላ ደብዳቤ አረዱን። እርማችንን ተንሰቅስቀን፣ ተንቀጥቅጠን አወጣን።

አባቴ እና ወንድሜ ሞቱ። ነገር ግን ለሞታቸው መታሰብያ የሞቱለት ጨለማን የማውደምም ሆነ ብርሃን የማፈንጠቅ ሂደት አልተከናወነም።

የቤታችን ሁለት የሙቀት ምስሶዎች ተገንድሰው ያለ ሙቀት፣ ያለ ምሰሶ እንኖራለን!
እኔ ስሜ ብርሃኑ ቢሆንም እናቴ ብርሃኔ ነው የምትለኝ፡፡ “ብርሃኔ” ስትለኝ 'ኔ' ን እርግጥ ጫን አድርጋ ስለምትጠራኝ የሆነ ማያዬ፣ እይኔ፣ ጧሪዬ የምትለኝ ነው የሚመስለኝ።

እንደ መርፌ ቀዳዳ አንድ ሆኜባት የኑሮ ፍልስፍናዋ በእኔ እና በኔ ዙሪያ ያጠነጥናል። ትንሽ ካመሸሁ ሰቀቀኗ ልክ የለውም። ሁሉም ነገር በሷ ሐሳብ ልክ ብቻ መሆን አለበት። አስራ ሁለት ሰዓት ቤት መግባት አለብኝ። አንድ ደቂቃ ካለፈ ስልኬ ይጮሃል። ቤት ገብቼ የማወራቸው ወሬዎች ከሀገር፣ ከመንግሥት፣ ከፖለቲካ የራቁ መሆን አለባቸው። በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ለፖለቲካ ቀረበ፣ ለሀገር መቆርቆር ስሜት ያለው ወሬ ማውራት አልችልም።

“ብርሃኔ አደራህን አታምሽ፣ በማያገባህ አትግባ፣ በፖለቲካም ቢሆን፤ ደ'ሞ ደ'ሞ ፖለቲካ ሽንፍላ ነው አይጸዳም፤ የራስ ወዳዶች መጠቀሚያ ቃታ ነው፤ የግል ችግሩን እኛ እያለ እየቸረቸረ ዝና እና ፍራንክ የሚለቅም ብቻ ነው ያለው፡፡"

ሐሳብ ከሐሳብ አይፋጭም። እኔ ልብላው፣ እኔ ካልበላሁት በሚል ይናጫሉ እንጂ ትግሉ የሐሳብ፣ ለሕዝብ ጥቅም የቆመ አይደለም፡፡ ሕዝብ ሕዝብ የሚሉት ለቲፎዞ ነው። አየህ ልጄ በፖለቲካ ጥሩ የደደበው ያሸንፍና ሥልጣን ይይዛል። ትዕቢት የወጠረው ደግሞ ይወድቃል፤ እኔ የማውቀው እና ያየሁት ፖለቲካችን ይሄ ነው፤ እንዳትበላብኝ አበባዬ።

ይሄውልህ ብርሃኔ ብሔር፣ ጎሳ፣ ዝምድና የፖለቲካችን መሠረት ነው። በእሱ ትሰባሰባለህ፣ ሴራ፣ ውሸት፣ ሆድ፣ ክሕደት፣ ድድብና አለው፡፡ ዓለሜ የታላቅነት እውነተኛ ሕልም፣ እውቀትህ ያስበላሃል። እውነተኛ ከሆንከ ያሴሩብሃል፣ ያድሙብሃል፣ ስምህን ያጠለሹታል። የማያውቅህ ወታደር ጥንካሬውን ይፈትሽብሃል ወይ ደግሞ እንዳባትህ እና ወንድምህ ግንባርህን ይልሃል።”

"ፖለቲካችን ሞት አለው፤ ካልጨከንክ፣ ካልደደብክ መከራ ይጥልብሃል፣ ያሻህን ተናግረህ አትኖርም፣ አትወጣም፣ አትገባም፣ ሚስትህን ባል አልባ፣ ልጅህን አባት ታስናፍቀዋለህ። ቂመኛ ነው ቀን ይጠብቅልሃል። እንደኔ ባል እና ልጅ እንዳንተ አባት እና ወንድም ደቼ ትበላለህ።

ብርሃኔ እኔ ልሙት እልሃለሁ ፖለቲካችን ውስብስብ አይደለም። ለመጉላት ደደብ እና ራስ ወዳድ መሆን መስፈርቱ ነው። የሚወደድ ነገር የለውም፡፡

አበባዬ የሚፈልጉትን የሚያጎሉት እና የሚያፈዙት እነርሱ ራሳቸው ናቸው። ይሄውልህ ብርሃኔ በዚህ ጸድቶ በማይጸዳ ፖለቲካ ብትሞትብኝ ለአንድ ሳምንት ብሶቴ፣ እንባዬ፣ ለቅሶዬ በየሰፈሩ በየካሜራው ይንከባለላል። ከዛ... ይረሳል፤ ሐዘኑ እና ስብራቱ እኔ ጋ ብቻ ይቀራል።


ብርሃኔ የተበላሸ ሂደት ውስጥ ትክክል መሆን ስሕትት ነው!!
ልጄ የዚህ ሀገር ፖለቲካ ይቅርብህ፤ ትበላብኛለህ። አንዲት ጣት ማጣት ለማይገባው ዓላማ ባል እና ልጄን ገብሬያለሁ። ይበቃኛል።

ዜናው፣ ትግሉ፣ ፕሮፖጋንዳው፣ ጽንፈኝነቱ ከሰውነት ማማ ላይ ያወርዳል።
አደራህን ዓለሜ ግርግር ስታይ ለማጣራትም ብለህ ቢሆን እንኳን አትገተር። አትቀላቀል፤ ፖለቲከኞች ለግል ጥቅም ነው ተናጭተው የሚያናጩት። ሕዝብ ጥቅም ማግኛ ቃታቸው ነው። ችግሩ ወደ አንተ ካልመጣ አንተ ወደ ችግሩ አትሂድ።”
ከእናቴ የተለየ ሐሳብ ባይኖረኝም ያጣችውንም ስለማውቅ ስትናገር ጣልቃ ሳልገባ እሰማታለሁ፡፡
ዛሬም አባቴን እና ወንድሜን የበሉት ጅቦች ይጮኻሉ። ፕሮፖጋንዳቸውን ይነዛሉ። አንዱ ጎራ “ተነስ ከእኔ ጋ ብርሃን፣ ሰላም፣ ብልጽግናን በጋራ እናምጣ” ሲል አንዱ ጎራ “ሁሉም ሰላም ነው ተኛ! ዋ!” ይለኛል። ሁለቱም ጎራ እያንዳንዱን ክስተት ሥልጣን ማቆያ እና ሥልጣን መጨበጫ እንድትሆን አድርገው ይቀነብቧታል። ለሁሉም ና ከእኛ ጋ ሁን ጥሪዎቻቸው መልሴ ግን አንድ ነው፡፡

ወንድሜን እና አባቴን መልሱልኝ እና!!!

መፅሀፍ- አዎ እሱጋ ያመኛል
ደራሲ - አድሀኖም ምትኩ
share& Join
@Human_Intelligence
12.8K views17:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-12-15 07:16:21 እያንዳንዱን ችግር እንደ መሰላል ከተወጣጣህበት ከስኬት ጫፍ ትደርሳለህ!!

በአንድ ወቅት አንድ ገበሬ አህያው ጉድጉድ ወስጥ ትገባበታለች፡፡ ጉድጓዱ ሩቅ ከመሆኑ የተነሳ አህያዋ ለመውጣት በእጅጉ ተቸገረች፡፡ በጣም መጮህ ጀመረች፡፡ ባለቤቱም እሷን ለማውጣት ብርቱ ሙከራ አደረገ አልተሳካለትም ፤ አህያዋ አርጅታለችና ጉድጓድ ውስጥ ሊቀብራት አሰበ።

ጎረቤቶቹንም ጠራና ጉድጓዱን በአፈር መሙላት ጀመረ፡፡ አህያዋ ይህንን ስተመለከት እየቀበራት መሆኑን ተረዳችና እጅጉን  አዘነች፡፡

ይሁን እንጂ አፈር በተደፋባት ቁጥር አህያዋ አንድ ነገር ታደርግ ነበር። አፈሩን እያራገፈች ከአፈሩ ውስጥ ብቅ ትል ነበር። በተደጋጋሚ ከዚያም በተደፋው አፈር ላይ መቆም ትጀምራለች። በሒደት ውስጥ በአፈሩ ላይ በቆመች ቁጥር ከነበረችበት ጉድጓድ ከፍ እያለች በመጨረሻም ከጉድጓዱ ውስጥ ሙሉ በሙሉ መውጣት ቻለች፡፡ በሚገርም ሁኔታ አህያዋን ሊቀብሯት የሞከሩት ስዎች ሁሉ በአህያዋ አወጣጥ በእጅጉ ተደነቁ፡፡

ውድ አንባቢያን እንደሚታወቀው የአህያዋ ታሪክ ሁላችንንም ይመለከተናል። የሚጫንብን አፈር ደግሞ በየጊዜው የሚያጋጥሙንና ዝም ብንላቸው በመጨረሻ ሊቀብሩን የሚችሉ ችግሮች ወይም መሠናክሎች ናቸው፡፡ አፈሩን የሚጭኑት ሰዎች በዙሪያችን ያሉ ሰዎች፣ ነገሮች፣ በህይወታችን ላይ ተፅዕኖ የሚፈጥሩብን አዳዲስ ለውጦች እንዲሁም የራሳችን አፍራሽ ስሜቶች ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ጉድጓዱ ደግሞ አሁን ያለንበት ግራ የተጋባንበት! ተስፋ ቢስ የሆንበት፡ መላ ያጣንበት ህይወት ወይም ገጠመኝ ሊሆን ይችላል፡፡

በእርግጥም እኛ ሰዎች በጤናችን! በኢኮኖሚ ህይወታችን፤ በትዳርና ፍቅር ህይወታችን በተለያየ አጋጣሚ ልክ እንደ አህያዋ ጉድጓድ ውስጥ የመግባት ዕድላችን ቀላል የሚባል አይደለም፡፡ ይሁን እንጂ ጠንካሮች እንደ ጠንካራዋ አህያ ከገቡበት ጉድጓድ ውስጥ መውጣት ሲችሉ አንዳንዶቹ በዚያው ተቀብረው ቀርተዋል፡፡

ውድ አንባቢያን በህይወታችን ውስጥ ያለው አማራጭ! ወደ ላይ መውጣት አልያም ደግሞ ወደ ታች ወርዶ ከጥልቅ ጉዳጓድ ውስጥ ተቀብሮ መቅረት ብቻ ነው! በየጊዜው ሊገጥመን የሚችለውን ችግር ልክ እንደ አህያዋ የሚጫንባትን አፈር እየረገጠች ወደ ላይ ከፍ እንዳለችው ሁሉ አንተም/አንቺም በየጊዜው የሚገጥማችሁን ችግሮች እንደ ድጋፍ እየተጠቀማችሁ በጥንካሬ ወደ ላይ መነሳት ያስፈልጋል፡፡ ከጥልቁ ጉድጓድ ውስጥ ለመውጣት የምንችለው ለመውጣት የምናደርገውን ጥረት ባለማቆም ብቻ ነው።
በመሆኑም ምንጊዜም በጠንካራ ውስጣዊ ቁርጠኝነትና እምነት ችግሮችን እንደ መወጣጫ ደረጃ በመጠቀም ከታች ወደ ላይ ተጓዙ ለማለት እወዳለሁ።

#share
Join: @Human_Intelligence
12.8K views04:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-11-22 21:06:42 የጠፋውን የሰው ልጅ ፍለጋ (Search for the lost human soul)

ዘመኑ 1950ዎቹ ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ... ከሁለቱ የዓለም ጦርነቶች ስካር የባነነው ዓለም ለሌላ ዓይነት ባርነት ራሱን ሲያዘጋጅ ተገኘ፡፡ ሥልጣኔውም አገዘው፡፡ የሥልጣኔ ቀዳሚው ተልዕኮ የሰውን ልጅ እንሰሳዊ ደመነፍስ ማላመድ (taming human animalistic aggresion) ቢመስልም ውጤቱ ግን የተገላቢጦሽ ሆነ፡፡ ለኤሮፓዊ ፋውስታዊ የዛገ መዳዳቱ ስምረት ቴከኖሎጂው ረዳት ሆነለት፡፡

ዘመኑ ሰው ወደ አሻንጉሊትነት የሚያደርገውን የመምዘግዘግ ጉዞ አሀዱ ያለበት ሆነ፡፡ በአዲሱ ፈጠራ ቴሌቪዥን በመታገዝ "ፖፕ ከልቸር" ሰለጠነ፡፡ ሁሉም አብረቅራቂው ዘመን አመጣሽ ሳጥን ጋር ፍቅር ወድቆ ለአዲሱ ጊዜ ባርነት ራሱን አዘጋጀ፡፡ ዓመታት ተቆጠሩ፡፡ ቴክኖሎጂው በቀኝም በግራም እኩል ይመነደጋል፡፡ ቫይረሱ እና አንቲቫይረሱ፣ ሚሳኤሉና ጸረሚሳኤሉ እኩል ይበለጽጋሉ፡፡

ዛሬ ከሰባ ዓመታት በኋላ በዓለምአቀፍ ደረጃ ወደ ሁለት ቢሊዮን የሚጠጉ የቴሌቪዥኖች ዝግጅቶች ፣ ከ5 ቢሊዮን በላይ የሞባይል ስልኮች በሰው ልጆች እጆች ላይ ይገኛሉ። በአንጻሩ በሰው ልጆች የንባብ አትሮኖሶች ላይ እንደተዘረጉ የሚገመቱት መጻሕፍት ዓይነት ከ150 ሚሊዮን አይበልጥም፡፡

እነሆ ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ሞታችን ረክሶ ‹ላይቭ ስናየው ስንኳ ማስደንገጡ ቀንሷል፡፡ እንበላለን፤ ግን አናጣጥምም፡፡ እንዋሰባለን፤ ግን ፍቅርን ረስተናል፡፡ አብረን ሆነን ለብቻችንን ነን፡፡ አብረን እየኖረን አንዳችን ለሌላችን በዓድ፣ ሩቅ ነን፡፡ ወዳጅነት፣ ሣቅ፣ ፈገግታ፣ መታመን፣ ፍቅር፣ ፍትወት... ሸቀጥ ሆነው በገበያ ዋጋ ይቸበቸባሉ፡፡

ሰብዓዊት የማይቀለበስበት አስፈሪ ውጥንቅጥ ውስጥ ገብቷል፡፡ አንዳንዶች ይህ አረዳድ ጭፍንነት ሊመስላቸው ይችላል፡፡ አንዳንዶች ሀዘኑ ቤታቸው እስኪገባ ድረስ የመቃብር ደወሉ በየዕለቱ ለእነርሱ እንደሚደወል ይረሱታል፡፡

እናስ ኤሪክ ፍሮም እንዳስጠነቀቀው የሚቀጥለው ዘመን ሮቦቶች ለመሆን ምን ያክል ይቀረናል? በዚያ ዘመን (በ195oዎቹ አጋማሽ) የተነሱት እንደ ኤሪክ ፍሮም ዓይነት የሰው ልጅ ዕጣ ያስጨነቃቸው አሰላሳዮች ሰው ስለመዳረሻው እንዲጠነቀቅ አብዝተው ቢወተውቱም ሁሉም ከአጥበርባሪ ሳጥኗ ጋር ሲወዛወዝ ሰሚ አልነበራቸውም፡፡ ኤሪክ ፈሮም በ1955 እ.ኤአ በታተመ The Sane Society› በተሰኘ መጽሐፉ ላይ እንዲህ አለ፡፡

‹የ19ኛው ክፍለዘመን ጥያቄ፣ ትርክት ‹‹እግዚአብሔር ሞቷል›› ነበር፡፡ የሀያኛው ክፍለዘመን ፈተና ግን የሰው ልጅ ሞቷል› ሆነ፡፡ በ19ኛው ክፍለዘመን ኢ-ሰብዓዊነት ማለት ጭካኔ ነበር፡፡ በ20ኛው ክፍለዘመን ግን ኢሰብዓዊነት ማለት መደንዘዝ፣ ስሜት ማጣትና መነጠል ሆነ፡፡ የትናንት ስጋታችን የሰውን ልጅ ወደ ባርነት እንዳይገባ ነበር፡፡ የነገ ስጋታችን ግን የሰውን ልጅ ከሮቦትነት የመታደግ ሆኗል፡፡››

‹‹ሁላችንም በዘመናዊው የምዕራብ ዓለም የምንኖር ሰዎች እብደት ውስጥ ነን፡፡ ራሳችን እያታለልን ላለመሆናችን ምን ዋስትና አለን?››

ዓለም መልክ የሌለው መገማሸር ውስጥ ገብታለች፡፡ ልክ አንደ ሁልጊዜው!... በዚህ ሂደት ሰው የመሆናችን ቀለም አጥተናል፡፡ ሰው የመሆናችን ውሉ በምን ይረጋገጥ? ከቅድመ አያቶቻችን የሚያስተሳስረን ፈትለነገር ከተቋረጠ ሺህ ዘመናት አልፈዋል፡፡ በሕንጻ ሰንሰለቶች መካከል እየተመላለስን ስንኳ ሕልማችን የተራራ፣ የሸንተረር፣ የአደን፣ የለቀማ ነው፤ እንደ ግዞተኛ ነን፤ ፊሊፒናዊ፣ ቼካዊ፣ ቱርካዊ... መሆናችን፣ የመጽሐፍ ቅዱስ፣ የቅዱስ ቁርዓን፣ ወይም የማናቸውም ቅኝት ሥሪት መሆናችን እውነታውን አይቀይረውም፡፡

እኔ ግን የዓይኑ ቀለም ያላማራቸውን በጅምላ ኮንነው ሰልፊ እየተነሱ ዘቅዝቀው የሚሰቅሉ ሕዝቦች ሀገር ዜጋ ነኝ፡፡ ያ ሁሉ የሺህ ዘመናት ወንጌል፣ ሥነምግባር፣ ሀፊዝ፣ ሥርዓት፣ ትምህርት፣ ግብረገብነት በቅፅበት ውኃ በልቶት መቅላት፣ እስከነፍስ ማቃጠል፣ መደፍጠጥ፣ ማሳደድ... ሁሉም በሚያስደነግጥ ፍጥነት ሲከናወን አቅመቢስ ስዱድ፣ ዲዳ ሆኘ ተመልከቻለሁ፡፡ ታምሜያለሁ፡፡ ብዙ ኢፍትሃዊነት ባለበት ምንም ማድረግ ካለመቻል በላይ የሚያም ምንስ ነገር ይኖራል?

ለነገሩ በየትኛውም የዓለም ክፍል በሰብዓዊነት፣ በአጠቃላይ በስነፍጥረት ላይ የሚቃጣ በደል ካላመመኝ የስካሩ አካል ሆኛለሁ ማለትም አይደል? አንዳንዶች ለዚህ መድኃኒቱ ዜግነትን ማስረጽ፣ ሕገመንግስት መቀየር... ዓይነት _ ጨዋ ሐሳቦችን ሲሰነዝሩ እሰማለሁ፡፡ ምንኛ የዋሆች ሆነዋል ጃል! የታመመው በአጠቃላይ የሰው ልጅ (ሰብዓዊነት) መሆኑን ማየትስ እንዴት ይሳናቸዋል? ይህ የሰብዓዊነት ማሽቆልቆል፣ ስርዓት በመቀየር፣ ደንደሳም ዴሞክራሲ በማስረጽ፣ በአዋጅ በማስነገር፣ ኢትዮጵያን እንደ አሜሪካ በማበልጸግ ብቻ ሊሻሻል አይችልም፡፡ እንዲውም ሁላችንም ከጫፍ እስከ ጫፍ እንደ ሰው ካላሰብን አንተርፍም፡፡


ዘመናዊው የሰው ልጅ ከቅድመ አያቶቻችን አንጻር የሁሉም ነገር ውስጥ መትረፍረፍ ውስጥ ነው፡፡ ዛሬ የአንድ አሜሪካዊ ቤተሰብ አማካይ የመገልገያ ቁሳቁሶች ብዛት እስከ 300,000 ይገመታል፡፡ ከመቶ ዓመታት በፊት ከነበረው ጋር ሲነጻጸር 5000% እጥፍ ተመንድጓል፡፡ ዘመኑ በሁሉም ነገር የመትረፍረፍ (Abundance) ቅዠት ውስጥ የሚዳክር ይመስላል፡፡ ነገርግን መትረፍረፍ መቅሰፍት ሆኖብን ምኞታችን፣ እውነታችን፣ የሕይወት ትርጉማችን አሳክሮብናል፡፡ ምንም የማይፈይድልን የመረጃ ናዳ ያጥለቀልቀናል፡፡ በተሳከረ የመረጃ ቱማታ ተዋክበን እውነታችን ራሱ ዋጋ አጥቷል፡፡

ዘመኑ እንደየትኛውም ግልብ ዘመን ነበርና ኤሪክ ፍሮምና መሰሎቻቸው አድማጭ አላገኙም፡፡ እንደየትኛውም ዘመን... ዛሬ ለስሙ እንሰዋለን የሚሉ ቢሊዮናት ተከታዮች ያሉት መሲሁ በቁርጡ ቀን ከመስቀሉ ፊት ለፊት ለብቻው እንደነበረበት ዘመን፡፡ የሚያሳዝነው ዘመን ልብ መግዛት ሲጀምር ዕድሎች ቁጭት ሆነው ከተፍ ማለታቸው እኮ ነው፡፡

የሰው ልጅ የለየለት ዕብደት ውስጥ ገብቷል፡፡ ነጠል ብሎ ለሚታዘብ ተመልካች የሚታየው የሚሰማው  ሁሉ  አጃኢብ ነው፡፡ ሥልጣኔው ሁሉ በየዕለቱ የሚያስመዘግበው መካን፣ መራቀቅ የአውዳሚነት መሆኑ ተስፋ ያስቆርጣል፡፡ ከጦር መሣሪያ ጋር ያልተነካካው ቴክኖሎጂያዊ ፈጠራ ስንኳ በየዕለቱ ሰብዓዊነትን የሚያኮሰምን የመሆኑ ነገር ያስደነግጣል፡፡

ተመራማሪዎች በቅርቡ ሰው በማይደርስባቸው አስፈሪ የአርክቲክ አካባቢዎች ሳይቀር ብዙ ሺህ ቶን የሚመዝን የማይበሰብስ ቆሻሻ አግኝተዋል፡፡ የሰው ልጅ አሁን በተያያዘው ግዴለሽ ጎዳና ከቀጠለ ሩቅ በማይባል ዘመን ሕይወት ከውቅያኖሶችና ባህራት ተጠቃልሎ ሊጠፋ ይችላል፡፡


በፍም እሳት መቃመስ
ያዕቆብ ብርሀኑ

ይቀጥላል
@Zephilosophy
13.0K views18:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ