የፋሽስቱ ቡድን በትግራይ ላይ ዳግም የፈፀመውን ጥቃት በጣም እንዳሳዘናቸው የአሜሪካ ምክር ቤት አባል ኮንግረስ ማን ብራድ ሼርማን ገለፁ። በአለማችን የከፋው ሰብአዊ ቀውስ እየተጋፈጠ ያለው የትግራይ ህዝብ አሁን ላይ እንደ አዲስ የተከፈተበት ጥቃት ለረሃብ የተጋለጡ በሚልዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች ወደ ከፋ አደጋ የሚጥል ነው ብለዋል ኮንግረስ ማን ብራድ ሼርማን በቲዊተር ገፃቸው ባሰፈሩት መልእክት። ኮንግረስ ማን ብራድ ሼር ማን አክለውም የአሜሪካ መንግስት በአስቸኳይ ተኩስ የሚቆምበት ሁኔታ እንዲፈጠርም አሳስበዋል። ነሓሴ 19/2014 ዓ/ም ድምፂ ወያነ ትግራይ 1.8K views16:14