Get Mystery Box with random crypto!

የጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ እውነተኛ ደጋፊዎች

የቴሌግራም ቻናል አርማ abdisira — የጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ እውነተኛ ደጋፊዎች
የቴሌግራም ቻናል አርማ abdisira — የጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ እውነተኛ ደጋፊዎች
የሰርጥ አድራሻ: @abdisira
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.46K

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-12-23 21:59:34
"የሀገር ግንባታ ላይ ሚዲያ ጉልህ ሚና አለው"

የአራዳ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት በክፍለ ከተማው ከሚገኘው የኦሮሚያ ወጣት ማህበር ጋር በማህበራዊ ሚዲያ እና በሌሎች የኮሙኒኬሽን አግባቦች መረጃዎችን ለህብረተሰቡ ማድረስ በሚቻልበት ሁኔታ ዙሪያ መወያየታቸውን አስታወቀ፡፡

የአራዳ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ በላይነህ ሙሉጌታ የተግባቦት ደረጃን ከፍ ለማድረግ ለኦሮመኛ ቋንቋ ተናጋሪ የማህበሩ አባላት በማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀምና በኮሙኒኬሽን ስራዎች ዙሪያ ግንዛቤ ወስደው ወደስራ እንዲገቡ ስልጠና መስጠቱ አስፈላጊ ነው ብለው በቀጣይም ከአምስት በላይ በሚሆኑ የሀገራችን ቋንቋዎች መረጃዎችን በማድረስ ህብረ ብሔራዊ በሆነ መልኩ እንሰራለን ብለዋል፡፡

በአብዛኛው የክፍለ ከተማችን ወጣቶች ጥያቄ መሰረት በኦሮምኛ ቋንቋ የሚዲያ አማራጭ የከፈትን ሲሆን ሚዲያ አጠቃቀም ላይ በጋራ ልንሰራ ይገባል ያሉት አቶ በላይነህ ትክክለኛና ብቃት ያለው የኮሙኒኬሽን ሰራዊት የሚባለው ሁሉንም በእኩል የሚያይና ሀሰተኞችን በትክክለኛ መረጃ የሚመክት ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡

በአራዳ ክፍለ ከተማ የኦሮሚያ ወጣት ማህበር ሰብሳቢ ታደሰ ኪላ መረጃዎች ወደ ህብረተሰቡ እንዲደርሱ ከማድረግ አንፃር በአፋን ኦሮሞ መረጃ ማስተላለፍ መጀመሩ ተደራሽነትን የማሳደግ ሚናው የጎላ ነው ብለው ሁላችንም ባሉን ስማርት ስልኮች አማካኝነት ትክክለኛውን መረጃ ከትክክለኛው አካል ወስደን ማጋራት አለብን ብለዋል፡፡

በመጨረሻም ከክፍለ ከተማ እስከ ብሎክ ድረስ የኮሙኒኬሽን ሰራዊት ግንባታ ላይ ውጤታማ ስራ በመስራት ላይ እንገኛለን ያሉት አቶ በላይነህ ሚዲያ ዘመናዊ የትግል ሜዳ እንደመሆኑ በሄዳችሁበት ሁሉ ሰላም፣ ፍቅርና አንድነትን ስበኩ ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
386 views18:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-23 16:14:02 አቶ መለሰ ዓለሙ በአራዳ ክፍለ ከተማ በልዩ ሁኔታ በ90 ቀናት እየተከናወኑ ያሉ ስራዎችን ተዘዋውረው ተመለከቱ

የብልፅግና ፓርቲ አዲስ አበባ ቅርጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መለሰ ዓለሙ በአራዳ ክፍለ ከተማ በልዩ ሁኔታ "አራዳን እንደገና" በሚል በ90 ቀናት እየተከናወኑ ያሉ ሰው ተኮር የልማት ስራዎችን ያሉበትን ደረጃ ተዘዋውረው ተመልክተዋል።

"አራዳ እንደገና" በሚል ከተያዙ የልማት ፕሮጀክቶች በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ተግባራት በእቅድ መሰረት ተጠናቀው አገልግሎት እንዲሰጡ ለማስቻል እየተደረገ ያለ የአመራር ድጋፍና ክትትል በመስክ ተገኝተው ጎብኝት አከናውነዋል።

የአገልግሎት አሰጣጥ ጋር ተያይዘው የሚታዩ ችግሮችን ለመቅረፍ የተቋማትን ምላሽ የመስጠት አቅም ለመፍጠር የተጀመሩ ስራዎችም የጉብኝቱ አካል ነበሩ፤ በወረዳ 06 በሚገኘው ጃንሜዳ ጤና ጣቢያ እየተከናወነ ያለውን የአገልግሎት አሰጣት የማሻሻል ስራ የተመለከቱት አቶ መለሰ የጤና ተቋሙን በ90 ቀን በሰው ተኮር ስራዎች ተቋማትን ሞዴል ለማድረግ የተጀመሩ ስራዎች በተቋሙ ያለቱን ቦታዎች በአግባቡ በመጠቀም እና አገልግሎትን በማዘመን የተገልጋይ እንግልት የሚያስቀር ወጪና ብክነት ቀናሽ እንዲሁም የቁጥጥር ስራ የሚያቀላጥፍ ብሎም ሌብነትን የሚገታ ወረቀት አልባ አገልግሎት ጅምር አበረታች እንደሆነ ተመልክተዋል።

በጤና ተቋሙ ለሚመጡ መስማት ለተሳናቸው ተገልጋዮች አገልግሎት መስጠት እንዲያስችል የምልክት ቋንቋ ስልጠና ለተቋሙ ሰራተኞች እየተሰጠ መሆኑን የተመለከቱት አቶ መለሰ ይህ አይነት ተግባር አካል ጉዳተኞችን ለማገልገል ያለውን ተነሳሽነት የሚያመለክት በመሆኑ ይህ ተግባር በሌሎች አገልግሎት ሰጪ ተቋማት በተሞክሮ መልክ ለመስፋት የሚያግዝ መሆኑን ተናግረዋል።

በክፍለ ከተማው ወቅታዊ የፀጥታ ስራ መልካም አፈፃፀም የታየበት ሲሆ በ90 ቀን የሚከናወኑ ሰው ተኮር የልማት ተግባራት በተያዘላቸው ጊዜ እና በፍጥነት ለማጠናቀቅ አመራሩ የሠላም የልማትና የመልካም አስተዳር ስራዎች ጎን ለጎን አስተሳስሮ የመስራት ልምዱን የበለጠ ማጠናከር እንደሚገባው አቶ መለሰ አሳስበዋል።


የፌስ ቡክ ግሩኘ https://facebook.com/groups/1214264802267291/
467 views13:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-23 16:13:55
414 views13:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-23 16:03:17
በአንድ ወቅት ምንም ልማት ባልነበረበት የብላቴ ወንዝ ተፋሰስ፣ የከርሰ ምድር ውኃን በመጠቀም የተለያዩ የአትክልትና ፍራፍሬ ዝርያዎች እየተንዠረገጉበት ነው። በቆራጥ የግሉ ሴክተር ባለሀብቶች የሚለሙትን እርሻዎች የምርታማነት ዐቅም ለማየት ወደ ቦታው ተመልሰናል። የዚህ አካባቢ ምርታማነት ከክፍፍል ይልቅ ትብብር የሚያስገኘውን ውጤት ማሳያ ነው። ይህ ተሞክሮ በሀገር አቀፍ ደረጃ መስፋፋት አለበት።

ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ
482 views13:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-20 21:36:45
በውሸት ሁከት ለማስነሳት የሚሯሯጡትን ጭር ሲል አልወዶችንም አደብ ማስገዛት ግድ ይላል!

ስንታየው ቸኮል የሚባል ወያላ አጀንዳ ለመፍጠር ሲል ያልሆነውን ሆነ! ያልተባለውን ተባለ ይላል! ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተገኙበት የአዲስ አበባ አስተዳደር ስራ ተገመገመ የሚል ዜና ሰምቶ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያላሉትን ብለዋል በማለት ህዝብን እና መንግስትን ለማቃቃር እና ለማግጨት ሲል አይን ያወጣ ውሸትን አጋርቷል!

ስንታየው እንዲሁም ፓርቲው ባልዲራስ በከተማው ሰላም መስፈኑ እንቅልፍ የሚነሳቸው ከግጭትና ከሁከት ለማትረፍ ሲሉ የግጭት ነጋሪትን በተደጋጋሚ ይጎስማሉ! የኢትዮጵያ ሕዝብም ሆነ የከተማው ነዋሪ ከሰላምና ከአብሮነት እንጂ ሁከትና ብጥብጥ የሚገኝ ምንም አይነት ትርፍ አለመኖሩን ጠንቅቆ ያውቀዋል! የእነዚህ የግጭት ነጋሪት ጎሳሚዎች በትር መሆንንም አይምርጡም! በውሸት ሁከት ለማንሳት የሚሯሯጡትን አደብ ማስገዛት ግድ ይላል!

የቴሌግራም ቻናል https://t.me/abdisira
የፌስ ቡክ ግሩኘ https://facebook.com/groups/1214264802267291/
263 views18:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-20 15:59:41
ከተወሰኑ ወራት በፊት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር አመራሮችን ሰብስበዎ ነበር። በስብሰባውም ለቀጣይ 100 ቀናት ዕቅድ ተግባራዊ የሚደረጉ ጉዳዮችን አቅጣጫ ማስቀመጣቸው ይታወሳል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በድጋሚ ዛሬ በጽሕፈት ቤታቸው የመስተዳድሩን አመራሮች አግኝተው የከተማውን የ2014 በጀት ዓመት እና የ2015 ሩብ ዓመት አፈጻጸም ገምግመዋል። በመጨረሻም በከተማዋ የተጀመሩ መልካም የልማት ሥራዎችን እንዲስፋፉ፤ ችግሮችም እንዲስተካከሉ አቅጣጫ ሰጥተዋል።

የቴሌግራም ቻናል https://t.me/abdisira
የፌስ ቡክ ግሩኘ https://facebook.com/groups/1214264802267291/
376 views12:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-20 15:19:03
ብልፅግና ፓርቲ በትውልድ ቅብብሎሽ ሁለንተናዊ ብልፅግናን እዉን የማድረግ ራዕይ ሰንቆ የተነሳ ፓርቲ ነው።

ብልፅግናን በማረጋገጥ ሂደት ሠላም መሠረታዊ አስፈላጊ እሴት ነው።
የብልፅግናው ጉዞ አልጋ በአልጋ እንደማይሆን የሚጠበቅ ቢሆንም የጉዞውን ሂደት የሚያደናቅፉ፣ የጉዞዉን ፍጥነት የሚገቱ የሠላምና የደህንነት ስጋቶችን ምንጫቸዉን በተቻለ መጠን ማድረቅ አስፈላጊ ነው።

የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግናን የማረጋገጡ ራዕይ እዉን እንዲሆን ራዕይው የአብዛኛው ህብረተሰብ የጋራ ራዕይ እንዲሆን፣ አንፃራዊ የሆነ የዓላማና የተግባር መሰናሰልንና አረዳድ መፍጠር ይጠይቃል።

በዓላማና በተግባር የተጣመረ የቁጭት መንፈስ በመፍጠር ፀጋዎቻችንን በማልማት ዘላቂና ተከታታይ እድገት ብቻ ሳይሆን ብልፅግናን ለማረጋገጥ የተጀመረውን ጥረት ዘላቂ ለማድረግ ሠላም መሠረታዊ ነዉ። የፖለቲካ ስብራቶቻችንን በማረም የወንድማማችነት እና የእህትማማችነት እሴቶችን እና ትርክቶችን ማጎልበትም ለዘላቂ ሰላም ወሳኝ ነው።

በተለይም አካታች ሀገራዊ የምክክር ሂደቱ የልዩነት ሀሳቦችን በአንፃራዊነት አቀራርቦ የይቅርታና የፍቅር ድልድይ በመዘርጋት፣ ዘላቂ ሠላምን ማረጋገጥ የሚያስችል አይነተኛ መሣሪያ መሆኑን የተለያዩ ሀገራት ልምድ ያሳያል።

የአካታች ሀገራዊ የምክክር ሂደቱ እና ዉጤቱ የተሳካ እንዲሆን ማድረግ ማለት ጠንካራ ዲሞክራሲን እና ዘላቂ ሠላምን ኢትዮጵያ ውስጥ ማረጋገጥ ማለት ነዉ።

ሠላም በጋራ ጥረት የሚሳካ መሠረታዊ ጉዳይ በመሆኑ የጉዳያችንን ማዕከል የኢትዮጵያ ሠላም፣ ልማትና ዲሞክራሲ እንዲሆን በማድረግ፣ አንድ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ማህበረሰብ ለመገንባት ሰላም መሠረታዊ በመሆኑ ለዘላቂ ሠላም የየበኩላችንን ማበርከት አለብን።

የቴሌግራም ቻናል https://t.me/abdisira
404 views12:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-19 22:06:21
የያዝከው እውነት የአለምን ዳርቻ ተቆጣጥሮታል

ኢትዮጵያ በጀግናው መሪያችን አብቹ መመራት ከጀመረች አንስቶ ተቆጥረው የማያልቁ ድሎችን አስመዝግባለች! የብልጽግናችን ጥንስስ በአብቹ ሲጀመር ብዙ ተግዳሮቶች ነበሩት ዛሬ ግን በድል ጎዳና ላይ ሆነን አልበገር ባይነታችንን ለአለም እያሳየን እንገኛለን! እውነተኞች ሀቅ ይዘው ሲጓዙ በሀሰት ፕሮፖጋንዳ ሀገር ለማፍረስ የሚዳክሩት እጣ ፈንታቸው ውርደት እና ውድቀት ብቻ ነው! ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ የያዘው እውነት የአለምን ዳርቻ ተቆጣትሮታል።

የቴሌግራም ቻናል https://t.me/abdisira
የፌስ ቡክ ግሩኘ https://facebook.com/groups/1214264802267291/
514 views19:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-19 21:32:08
የአጡ ለተቸገሩ የሚሰጥ እጅ የተባረከ ነው!!

የአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 አስተዳደር ከብራይት ስታር ሪሊፍ ኤንድ ዴብሎመንት አሶሴሽን /WSG/ ጋር በመነጋገር በወረዳው ውስጥ የሚገኙ ደሀ ልጆችን ፣ሴቶችን እና ወጣቶችን በቀን 1 መቶ 30 ሰው መመገብ መቻላቸውን የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አወቀ ተስፉ ተናገሩ።
እንደ አቶ አወቀ ተስፉ ገለፃ ወረዳችን የከተማችን ብሎም የሀገራችን እምብርት ከመሆኖ አንፃር ከተለያዩ ሀገራት የመጡ ወጣቶች ማረፊያ መኖሪያም ናት ከዚህ የተነሳ በወረዳችን የሚኖር ብራይት ስታር ሪሊፍ ኤንድ ዴብሎመንት አሶሴሽን ጋር በመነጋገር እነዚህን ወጣቶችና ሴቶች ህፃናቶችን የመመገብ ስራ እየሰራን ነው ሲሉ ገልፀዋል።

የቴሌግራም ቻናል https://t.me/abdisira
የፌስ ቡክ ግሩኘ https://facebook.com/groups/1214264802267291/
482 views18:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-06 14:14:02
549 views11:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ